የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን በ2016 ዓ.ም የፌዴራል መንግሥት መ/ቤቶችን ለሁሉም ህጋዊ አቅራቢዎች/ነጋዴዎች/ተደራሽ ለማድረግ፣ የተቋማት ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከል እንዲሁም ሁሉንም አቅራቢዎች/ነጋዴዎች እኩል ለማሳተፍ የግዥ ሥርዓቱን በማዘመን ግልፅና ቀልጣፋ አሠራር በመዘርጋት ማንኛውም ግዥ በኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሥርዓት “eGP/electronic Government Procurement” ብቻ እንዲፈፀም መወሰኑ ይታወቃል፡፡

በዚሁ መሠረት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም ማንኛውንም ግዥ በኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሥርዓት /eGP/ ለመፈፀም ሙሉ በሙሉ ሥርዓቱን በመዘርጋት ተግባራዊ በማድረግ ላይ የሚገኝ በመሆኑ በአርባ ምንጭ ከተማና ዙሪያው የምትገኙ አቅራቢ ህጋዊ ነጋዴዎች በመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን ኤጀንሲ ምዝገባ በማድረግ በኤጀንሲ ድኅረ ገጽ ላይ በሚለቀቁ ግዥዎች ላይ እንድትሳተፉ ዩኒቨርሲቲው ያሳውቃል፡፡

    

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ

የብሩህ ተስፋ ማዕከል!

ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-

ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/

ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university

ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityCAD/

ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት