- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 2ኛውን ‹‹የአረንጓዴ አሻራ ቀን›› ከአርባ ምንጭ ከተማና ከጋሞ ዞን አመራሮች ጋር በመሆን ከሁለት ሺህ በላይ ችግኞችን በመትከል ግንቦት 28/2012 ዓ/ም በይፋ አስጀምሯል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ በ2011 ዓ/ም ክረምት በተደረገው የመጀመሪያው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ በስፋት መሳተፉንና በወቅቱ ከተተከሉ ችግኞች መካከል 94 በመቶ ያህሉ መፅደቃቸውን አስታውሰዋል፡፡Click her to see the pictures
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ከጋሞ ዞንና ከአርባ ምንጭ ከተማ አመራሮች ጋር በመሆን በ2011 ዓ/ም ‹‹በአረንጓዴ አሻራ ቀን›› የተተከሉ ችግኞች ያሉበትን ሁኔታ እንዲሁም የዘንድሮው ክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አስመልክቶ እየተደረጉ ያሉ የቅድመ ዝግጀት ሥራዎችን በቤሬ ተራራና በተለያዩ ችግኝ ጣቢያዎች በመገኘት ዛሬ ግንቦት 15/2012 ዓ/ም ጎብኝተዋል፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አምና ‹‹ በአረንጓዴ አሻራ ቀን›› ካስተከላቸው ችግኞች መካከል 94 በመቶው መፅደቃቸው ተገለፀ
- Details
Arba Minch University forthright in contributing in multiple ways to tackle crisis emerging from COVID-19 in the society has produced 1000 liters of sanitizers for health sectors rendering clinical services across its catchment. College of Natural and Computational Sciences’ Chemistry and Biology departments have played key role while the task was executed by University-Industry Linkage and Technology Transfer Directorate and its team.Click here to see the pictures
Read more: AMU produces 1000 liters of sanitizers for health sectors
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለጎፋ ዞን አስተዳደር የዞኑና የከተማው አመራሮች እንዲሁም የተለያዩ የአካባቢው ማኅበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት የኮሮናቫይረስን ለመከላከልና ለማከም የሚውሉ የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችን ግንቦት 5/2012 ዓ/ም አበርክቷል፡፡
የተደረገው ድጋፍ ለሳኒታይዘር ዝግጅት የሚውል 500 ሊትር አልኮል፣ 5 የሙቀት መለኪያዎች፣ ሰርጂካል የፊት መሸፈኛ ጭንብሎችና የእጅ ጓንቶች እንዲሁም ሌሎች የቫይረሱን ተጠቂዎች ለማከም የሚረዱ መድኃኒቶች ያካተተ መሆኑን የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺይፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ታምሩ ሽብሩ ገልፀዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለጎፋ ዞን አስተዳደር ኮሮናቫይረስን ለመከላከልና ለማከም የሚውል የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራንና ሐኪሞች አማካኝነት በጎፋ ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች ለተወጣጡ 60 የህክምና ባለሙያዎች በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከላከል፣ ቁጥጥርና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከግንቦት 4-5/2012 ዓ/ም ድረስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የቆየ ሥልጠና በሳውላ ከተማ ተሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጎፋ ዞን ለተወጣጡ 60 ህክምና ባለሙያዎች በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ