የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ የ2015 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ ቁልፍ የውጤት አመላካች (KPI) ላይ ነሐሴ 20/2014 ዓ/ም ከዩኒቨርሲቲው ም/ፕሬዝደንቶች ጋር የውል ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ሳይንስ ኮሌጅ ከተባበሩት መንግሥታት የምግብና እርሻ ድርጅት /Food and Agriculture Organization/ ደቡብ ቅርንጫፍ ጋር በመተባበር የሽፈራው/ሞሪንጋ ተክል ምርትና ምርታማነትን ማሻሻል፣ ግብይቱን ማሳደግ፣ የገበያ ትስስር መፍጠር እንዲሁም ዘርፉን በተሻለ ሁኔታ ማጠናከር ዙሪያ ከተለያዩ ክልሎች፣ ዞኖችና ወረዳዎች ለተወጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ከነሐሴ 18-20/2014 ዓ/ም የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ከተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን/The United Nations High Commissioner for Refugees (UNHCR) ጋር ባደረገው ስምምነት ኮንሶ፣ ደራሼ እና አሌ አካባቢዎች በግጭት ምክንያት ለተፈናቀሉ ዜጎችና መብታቸውን ለማስከበር አቅም ለሚያንሳቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ነፃ የሕግ ድጋፍ ለማድረግ ከመጋቢት 2014 ዓ/ም ጀምሮ ለአንድ ዓመት የሚቆይ ‹‹UNHCR-Arba Minch University Project›› የጋራ ፕሮጀክት አስጀምሯል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተከናወኑ የምርምር ሥራዎች ላይ ተመሥርቶ በጫሞ ሐይቅ ተፋሰስ ሥር በሚገኙ 10 ወረዳዎች ዘላቂ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ለማከናወን በጀርመን ልማት ባንክ፣ በኢትዮጵያ መንግሥት፣ በGIZ እና በማኅበረሰብ ተሳትፎ በሚሸፈን ከ1.8 ቢሊየን ብር በላይ በጀት የሚከናወንና ለ5 ዓመታት የሚቆይ ፕሮጀክት /Sustainable Land Management Project/ ይፋ ሆኗል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አቶ ዮናስ አስፋው ከአባታቸው ከአቶ አስፋው ማዳ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አስካለች ቦርቾ በቀድሞው ጋሞ ጎፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ወዜ ቀበሌ በ1981 ዓ/ም ተወለዱ፡፡