የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የባህልና ቋንቋ ጥናት ተቋም ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ‹‹ስነ-ቃል ለሀገራዊ መግባባት›› በሚል ርዕስ ግንቦት 13/2014 ዓ/ም ሀገራዊ ሲምፖዚየም አካሂዷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የ3ኛ ዲግሪ ምሩቃን በ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራም መማር ለሚፈልጉ በትምህርት ሂደቱ ዙሪያ ግንቦት 10/2014 ዓ/ም የልምድ ልውውጥ አካሂደዋል፡፡ 

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ግምገማና ትግበራ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በሁሉም ካምፓስ በሚገኙ የቅድመ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች የግለ ግምገማ ሰነድ አዘገጃጀት ዙሪያ ግንቦት 10/2014 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ት/ቤት የሰብዓዊ መብት ክበብ ለማቋቋምና በጋራ ለመሥራት ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከል ጋር በየዓመቱ እየታደሰ ለ3 ዓመት የሚቆይ የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ግንቦት 10/2014 ዓ/ም ተፈራርሟል፡፡ በዕለቱ የሰብዓዊ መብት ኮሚቴዎችም ተመርጠዋል፡፡