አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አሜሪካን ሀገር ከሚገኘው አላባስተር ኢንተርናሽናል/Alabaster International/ የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ዶርዜ ሆሎኦና ሃይዞ ለተወጣጡ 18 ሴት ወጣቶችና እናቶች ከእንሰት ቃጫ እሴት የተጨመረባቸውና ቱሪስትን ማዕከል ያደረጉ ጌጣጌጦችንና ሌሎች ቁሳቁሶችን ማምረት የሚያስችል ሥልጠና ከመጋቢት 9/2016 ዓ/ም ጀምሮ ለ15 ቀናት ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሁሉ አቀፍ ሴክተር ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ለዩኒቨርሲቲው የግብርና ሳይንስ ኮሌጅ የአስተዳደር ዘርፍ ኃላፊዎች በአእምሮ ውቅር ዙሪያ ከመጋቢት 18-20/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

 Arba Minch University organized the 10th Annual National Research Symposium on Science for Sustainable Development on March 30, 2024. Click here to see more photos.

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ፣ ግብርና ሳይንስ እና ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጆች በመተባበር 10ውን ሳይንስ ለዘላቂ ልማት ዐውደ ጥናት መጋቢት 21/2016 ዓ/ም አካሂደዋል፡፡ በዐውደ ጥናቱ ከተለያዩ የሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ ተመራማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን 18 ጥናታዊ ጽሑፎችም ቀርበዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡