- Details
‹‹የጠራ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ፖሊሲ፣ ስትራቴጂ፣ ዕቅድ፣ ፕሮግራሞችና ቁልፍ የውጤት አመላካቾች ግንዛቤና ትግበራ ለኢትዮጵያ ዕደገት፣ ልማትና ብልፅግና›› በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 10/2013 ዓ/ም ጀምሮ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በዋናው ግቢና ሳውላ ካምፓስ ከሚገኙ የካውንስል አባላትና ሠራተኞች ጋር የአሠልጣኝነት ሥልጠናዊ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
125ኛው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ‹‹ዓድዋ የኅብረ-ብሔራዊ አንድነት ዓርማ›› በሚል መሪ ቃል በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል፡፡ በሰላም ሚኒስቴር አማካኝነት ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ ዩኒቨርሲቲው በመምጣት ለ45 ቀናት በማኅበረሰብ አቀፍ የበጎ አገልግሎት ሥልጠና ላይ የቆዩ ወጣቶች ሽኝትም ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ባዮቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የእንሰት ምርት ሂደትን በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ እየሠራ ያለው ሥራ አበረታችና ሊሰፋ የሚገባው መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ተናገሩ፡፡ በምክር ቤቱ የሰው ሀብትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በዩኒቨርሲቲውና በኢንስቲትዩቱ በኢኖቬቲቭ እንሰት ፕሮጀክት አማካኝነት እየተሠሩ ያሉ ሥራዎችን ከየካቲት 27-28/2013 ዓ/ም በመስክ በመገኘት ምልከታ አድርገዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: የእንሰት ምርት ሂደትን በቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ የተጀመረው ሥራ አበረታች መሆኑን የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት ገለጹ
- Details
Arba Minch University has inked a memorandum of understanding with Ministry of Culture and Tourism and Ministry of Science & Higher Education wherein Ethiopian government has chosen AMU to launch a degree program on Translation and Interpreting; and modalities in this regard will be hammered out in a conference to be convened at Gamo Zone Culture Hall, Secha, on 2nd April, 2021. Representatives from universities, policy makers and different stakeholders are expected to participate, informs Director of Institute of Culture and Language Research (ICLR), Dr Seid Ahmed Mohammad.
Read more: AMU to launch degree in translation & interpreting, meet on 2nd April
- Details
ዩኒቨርሲቲው ከጋሞ ዞን ሰላምና ፀጥታ ግንባታ መምሪያ ጋር በመተባበር ‹‹ሁሉ አቀፍ የማኅበረሰብ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም›› በሚል መሪ ቃል በቁጫ ወረዳ ሰላም በር ከተማ የካቲት 24/2013 ዓ.ም የመጀመሪያ ዙር ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
ሥልጠናው ‹‹ሁሉ አቀፍ ማኅበረሰብ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ›› እና ‹‹በሃይማኖቶች መካከል መቻቻልና መከባበር›› በሚሉ ይዘቶች ዙሪያ መሰጠቱን የጋሞ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ የግጭት ዘላቂ መፍትሄ ሥራ ትግበራ ከፍተኛ ባለሙያና አሠልጣኝ አቶ መሰለ እንግዳ ተናግረዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ