Arba Minch University Senate in its 25th August, 2020, communiqué has stated that six of its senior academic staff members have been elevated to the position of Associate Professorship as all applicants found to be fulfilling required criteria thus confirming the key parameters stipulated by university rules and legislation.

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት በ25/12/2012 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ መርሃ ግብር በመደበኛ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 2,300 በላይ ተማሪዎች ቅዳሜ ነሐሴ 30/12/2012 ዓ/ም እንዲመረቁ ወስኗል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 503ቱ ሴቶች ናቸው፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Arba Minch University’s 33rd Convocation to be hosted virtually for its Master graduating class for 2020 at New Hall, Main Campus wherein a few will be officiating the ceremony led by university President, Dr Damtew Darza, Gamo Zone Administrator, Mr Birhanu Zewude, Jinka University President, Prof Gebre Entiso, Arba Minch Town Mayor, other invited guests & officials; while graduates, their near and dears and others can view it via online portals such as Facebook and YouTube from 8.30 onwards at their homes.

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት 39ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ከነሐሴ 21-23/2012 ዓ/ም ድረስ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለ3 ቀናት ተካሂዷል፡፡

መርሃ-ግብሩን በአገር ባህልና ወግ መሠረት መርቀው የከፈቱት የጋሞ አባቶች ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲዎች ሀገርንና ዓለምን የሚለውጡ አዳዲስ ሐሳቦችና ፈጠራዎች የሚፈልቁበት ቦታ እንጂ ተማሪዎች በቋንቋ፣ በብሄርና በሐይማኖት እየተከፋፈሉ የሚጣሉበት ሥፍራ እንዳይሆንና በተቋማቱ ከዚህ ቀደም እየታዩ የነበሩ የሠላም መደፍረሶች እንዳይከሰቱ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ የተማሪዎች ኅብረትና ሌሎችም የሚመለከታቸው ሁሉ አካላት ለሠላም ዘብ በመቆም የአገራችን ብልፅግና እንዲረጋገጥ በትኩረት እንዲሠሩ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከትምህርት ሚኒስቴር ለተገኙ ተወካዮች በባህሉ መሠረት ጥብቅ አደራ ከእርጥብ ሣር ጋር በመስጠት ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ የብሄር ማንነታችን የሚያብበው እንደ ሀገር ኢትዮጵያ ስትኖር ነው ያሉት አባቶቹ ሁላችንም ኢትዮጵያ በምትባል ምድር ላይ የተዘራን የሰብል ዓይነቶች በመሆናችን የሀገራችንን ህልውና ልናስጠብቅ እንደሚገባ በአጽንዖት ተናግረዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የፊዚክስ ትምህርት ክፍል በማቴሪያል ፊዚክስ የዶክትሬት ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራም ለመክፈት የውጭ ሥርዓተ ትምህርት ነሐሴ 18/2012 ዓ/ም ግምገማ አካሂዷል፡፡

የአካዳሚክ ጉ/ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ትውልድና የምርምር ዩኒቨርሲቲ እንደመሆኑ የ2ኛና 3ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞችን በማስፋፋትና በጥራት መስጠት ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሠራ የቆየ ሲሆን በፊዚክስ ትምህርት መስክ የሚከፈተው የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራምም የዚሁ ሥራ አካል ነው ብለዋል፡፡ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች ሲከፈቱ የሥርዓተ-ትምህርቱ ዝግጅት በርካታ ሂደቶችን እንደሚያልፍ የገለፁት ዶ/ር የቻለ ፕሮግራሞችን መክፈት በራሱ ግብ ባለመሆኑ ሥርዓተ-ትምህርቱን በየጊዜው የመከለስ እንዲሁም ትምህርቱን በጥራት መስጠትና ምርምር ተኮር የማድረግ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ በመሆኑ በቀጣይነት ይሠራል ብለዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ