ዩኒቨርሲቲው በምርምር የተገኘውን እንሰትን በዘመናዊ መንገድ ጥራቱን ጠብቆ ከ10 ቀናት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ለምግብነት ለማዘጋጀት የሚያስችል እርሾ በማምረት ለእንሰት አምራች አርሶ አደሮች ለሙከራ እያከፋፈለ መሆኑ ተገለፀ፡፡Click here to see the pictures

ዩኒቨርሲቲው የ2012 ዓ/ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብርን አስመልክቶ ለ2ኛ ጊዜ የፊታችን ሰኞ ሰኔ 8/2012 ዓ/ም ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የችግኝ ተከላ እንደሚያካሂድ ታውቋል፡፡ የችግኝ ተከላው በቤሬ ተራራ፣ በዩኒቨርሲቲው ስድስቱም ካምፓሶችና በመምህራን መኖሪያ አከባቢዎች ይፈፀማል፡፡Click here to see the pictures

Arba Minch University in association with Gamo Zone and Town Administration has celebrated ‘47th World Environment Day’ by planting thousands of saplings across its campuses and along town’s main street to Konso, at Secha, on 5th June, 2020. Arba Minch Mayor, Mr Sebsebe Bunabe, Education Sector Head, Mr Mado Mengesha, Environment and Forest Conservation Sector Head, Mr Tsegaye and AMU top officials including deans of colleges and directors participated in the event.Click here to see the pictures

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 2ኛውን ‹‹የአረንጓዴ አሻራ ቀን›› ከአርባ ምንጭ ከተማና ከጋሞ ዞን አመራሮች ጋር በመሆን ከሁለት ሺህ በላይ ችግኞችን በመትከል ግንቦት 28/2012 ዓ/ም በይፋ አስጀምሯል፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ በ2011 ዓ/ም ክረምት በተደረገው የመጀመሪያው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ በስፋት መሳተፉንና በወቅቱ ከተተከሉ ችግኞች መካከል 94 በመቶ ያህሉ መፅደቃቸውን አስታውሰዋል፡፡Click her to see the pictures

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ከጋሞ ዞንና ከአርባ ምንጭ ከተማ አመራሮች ጋር በመሆን በ2011 ዓ/ም ‹‹በአረንጓዴ አሻራ ቀን›› የተተከሉ ችግኞች ያሉበትን ሁኔታ እንዲሁም የዘንድሮው ክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር አስመልክቶ እየተደረጉ ያሉ የቅድመ ዝግጀት ሥራዎችን በቤሬ ተራራና በተለያዩ ችግኝ ጣቢያዎች በመገኘት ዛሬ ግንቦት 15/2012 ዓ/ም ጎብኝተዋል፡፡