AMU in association with Gamo Zone administration has jointly constituted Corona Task Force to prevent possible transmission of virus in the community. CTF has 40-member main committee with nine sub-committees to launch awareness campaign at zonal level, ensure sample testing; establish quarantine facilities to prevent further spread of virus and treatment aspect as well.

Gamo Zone Administrator, Mr Berhanu Zewde, heading CTF, said, all the committees will look into aspect such as communication, water sanitation, security, transport, etc. Zonal authority will contribute ETB 3 million and mobilize more resources in kind and cash from people across society, governmental and non-governmental organizations to support this social endeavor to tackle this catastrophe.Click here to see the pictures

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ስርጭት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተቋቋመው ግብረ-ኃይል ንዑስ ግብረ-ኃይል አባል የሆኑ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጤና ባለሙያዎች በአርባ ምንጭ ከተማ እንዲሁም በአርባ ምንጭ ዙሪያ፣ ጨንቻ፣ ካምባ፣ ገረሴና ቆጎታ ወረዳዎች በመገኘት በኮሮና ቫይረስ መከላከያ፣ መተላለፊያና ሊደረጉ በሚገባቸው ጥንቃቄዎች ዙሪያ ለአካባባቢው ማኅበረሰብ፣ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ አከናውነዋል፡፡

ግብረ-ኃይሉ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ እና በክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቺይፍ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ታምሩ ሽብሩ አማካኝነት በሲቀላ ገበያ በኮሮና ወረርሽኝ መከላከል ዙሪያ መጋቢት 25/2012 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክት እንዲተላለፍ አድርጓል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ እና የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጆች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚረዳ የንጽህና መጠበቂያ ሳኒታይዘር በማዘጋጀት ለዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ፣ ለኢንተርን ሐኪሞችና ለአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች እያሰራጩ መሆናቸውን ገለፁ፡፡ኮሌጆቹ ምርቱን በብዛት በማምረት ለአካባቢው ማኅበረሰብ ጭምር የማዳረስ ዕቅድ እንዳላቸውም ገልፀዋል፡፡

በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የባዮ-ቴክኖሎጂ መምህርና ተመራማሪ አቶ አዲሱ ፈቃዱ እንደገለፁት የንጽህና መጠበቂያው የዓለም ጤና ድርጅት ባስቀመጠው የአሠራር መመሪያ መሠረት የተዘጋጀ ሲሆን ምርቱም በዋናነት አልኮል፣ ግሊሲሮልና ሃይድሮጅን ፔርኦክሳይድ የተባሉ ንጥረ-ነገሮችን በመጠቀም የሚዘጋጅ ነው ብለዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቤኔፊት ሪያላይዝ (BENEFIT-REALISE) ፕሮግራም የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማስጠበቅና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በአርባ ምንጭ ክላስተር በምዕራብ አባያ፣ ደራሼ፣ ዛላና ቁጫ ወረዳዎች በሚገኙ 16 ቀበሌያት ምርጥ ዘሮችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ እያደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

የፕሮግራሙ አስተባባሪ ዶ/ር መብራቱ ዓለሙ እንደገለጹት የፕሮጀክቱ ዓላማ መልካም ተሞክሮዎችንና የተለያዩ ዝርያዎችን ከምርምር ጣቢያዎች በማምጣት የሴፍቲኔት ተጠቃሚ አርሶ አደሮች በምግብ ራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ነው፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ

AMU’s Water Technology Institute has signed 2-year joint project as part of the university cooperation for development of Flemish Interuniversity Council (VLIR) called, JOINT Project 2020 ‘Internet of Drops: Linking small water-related observations towards a cloud of data with IoT-enabled sensor networks’ with KU Leuven, Ecuador’s National Polytechnic School and Catholic University of Cuenca which is funded by VLIRUOS. Click here to see the pictures