የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ከሃንስ ሰይደል ፋውንዴሽን/ Hanns Seidel Foundation/ ጋር በትብብር ባዘጋጀው ዓለም አቀፍ ኮንፍረንስ ላይ ለመሳተፍ ከመጡ የተለያዩ ዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ተቋማት ጋር በሕግ፣ ፍትህ፣ ሰብዓዊ መብቶች፣ በስደት ዙሪያ በትብብር መሥራት በሚቻልበቻው አማራጮች ላይ ግንቦት 30/2014 ዓ/ም በኃይሌ ሪዞርት ውይይት ተካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ት/ቤት ከሃንስ ሰይደል ፋውንዴሽን/Hanns Seidel Foundation/ እና ከሰብዓዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር የምሥራቅ አፍሪካ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት (United Nations Human Rights Office of the High Commissioner, East African Branch) ጋር በመተባበር ‹‹አስገዳጅ ስደትና ፆታዊ ጉዳዮች በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ እይታ›› በሚል ርዕሰ ጉዳይ የመጀመሪያው ዓለም ዓቀፋዊ የምርምር አውደ ጥናት ከሰኔ 1-2/2014 ዓ/ም ድረስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ተካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት በ2013 እና 2014 በጀት ዓመታት ወደ መኅበረሰብ ወርደው ትግበራ ላይ የሚገኙ የምርምር ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ግምገማ ግንቦት 30/2014 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሰገንና ጨልኮ ወንዞች ላይ የመስኖ ውሃ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክቶች ዲዛይንና ጥናት ለማካሄድ ከደቡብ ዲዛይን፣ ግንባታና ቁጥጥር ባለሥልጣን ጋር ግንቦት 26/2014 ዓ/ም ባለ ድርሻ አካላት በተገኙበት የውል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ የሰገን ወንዝ በኮንሶ ዞንና በቡርጂ ልዩ ወረዳ መካከል ሲሆን የጨልኮ ወንዝ ደግሞ በመሎ ኮዛ ወረዳ በቦረዳ ጋዘር የሚገኙ ናቸው፡፡

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በሎጅስቲክ እና ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት ት/ክፍል መምህርና ተመራማሪ አቶ ሀቢብ ሳኖ “International Virtual Conference on Intelligent Computing in Humanity, Agriculture, Science & Technology” በሚል ርዕስ በተካሄደ ቨርቹዋል ኮንፈረንስ ላይ ቁልፍ ንግግር አቅርበዋል፡፡