የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ለ2014 ዓ/ም አዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች ከግንቦት 13-21/2014 ዓ/ም የሕይወት ክሂሎት ሥልጠና ሰጥቷል::ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ለሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ ለቴክኖሎጂና ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች አዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች ከግንቦት 19-20/2014 ዓ/ም አቀባበልና የላቀ ውጤት ላመጡ ነባር ሴት ተማሪዎች የሽልማት መርሃ ግብር አካሂዷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በደቡብ ክልል ከሚገኙ የተለያዩ ሆስፒታሎች ለተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች፣ የኦፕሬሽን ክፍል ነርሶች፣ አንስቴዥያ ባለሙያዎችና የሕክምና ዶክተሮች ከግንቦት 19-21/2014 ዓ/ም ‹‹ሰላማዊ የኦፕሬሽን ክፍልና የተሻለ የማገገም ሂደት/Safe Operating Room (OR) and Enhanced Recovery after Surgery Training›› በሚል ርዕስ ሀገር አቀፍ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ማኅበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ አስተባባሪነት በማሕፀንና ጽንስ ስፔሻሊስት ዶ/ር ነጋ ጩፋሞ የተመራ የሕክምና ቡድን በገረሴ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በመገኘት ለ4 አቅመ ደካማ እናቶች ነፃ የማሕፀን ውልቃት/መንሸራተት ቀዶ ጥገና ሕክምና አገልግሎት ግንቦት 19/2014 ዓ/ም ሰጥቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ‹‹Christian Aid››/ክርስቲያን ኤይድ/ ከተሰኘ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር የእንሰት አመራረትና ማብላላት ሂደትን ለማዘመን የሚረዱ በዩኒቨርሲቲው የተፈጠሩ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶ አደሩ ለማዳረስ 3.2 ሚሊየን ብር የተመደበለት ፕሮጀክት በትብብር እየሠሩ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የፕሮጀክቱን የሥራ እንቅስቃሴና አፈፃፀም አስመልክቶ ከድርጅቱ የመጣ ቡድን ግንቦት 16/2014 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ምልከታ አድርጓል፡፡