የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ት/ቤት ለ2013 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በመደበኛ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን እየመዘገባ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ የምዝገባ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን ባሳወቅነው ማስታወቂያ የመግቢያ ፈተና ጊዜ ወደ ፊት እንደሚገለፅ የተነገረ ሲሆን በዚሁ መሠረት ለሁሉም አመልካቾች የመግቢያ ፈተና የሚሰጠው በድህረ ምረቃ ት/ቤት ሕንፃ መስከረም 25/2013 ዓ/ም ከሰዓት ከ08፡00 ጀምሮ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ት/ቤት

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት