ለድህረ ምረቃ አዲስ አመልካቾች በሙሉ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ት/ቤት ለ2013 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በመደበኛ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን እየመዘገባ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

መስከረም 30 ዕለተ ቅዳሜ 2013 ዓ/ም ሊሰጥ የነበረው የድኅረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና ፈተናው የሥራ ቀናት ላይ እንዲሆን ከተለያዩ አመልካቾች ጥያቄ በቀረበው መሠረትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ምክንያት ፈተናው ለ3ኛ ጊዜ ለጥቅምት 09 ዕለተ ሰኞ 2013 ዓ/ም የተዛወረ መሆኑን ከይቅርታ ጋር እንገልፃለን፡፡

በዚህም መሠረት ተፈታኞች በተጠቀሰው ቀን የግብርና፣ የሕክምናና ጤና እንዲሁም የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ዘርፎች ተፈታኞች በኩልፎ፣ ነጭ ሣርና ዓባያ ካምፓሶች እንዲሁም በቀሩት ዘርፎች የምትፈተኑ በዋናው ግቢ የድኅረ ምረቃ ት/ቤት ሕንፃ ከጥዋቱ 03፡00 ጀምሮ በተዘጋጁ የመፈተኛ አዳራሾች በመገኘት እንድትፈተኑ እናሳውቃለን፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ት/ቤት

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት