የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ የዩኒቨርሲቲውን አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ከዩኒቨርሲቲው መምህራን መካከል አወዳድሮ ለመመደብ ይፈልጋል፡፡ አመልካቾች የትምህርት ደረጃቸው 2ኛ ዲግሪ እና ከዚያ በላይ ሆኖ ከማመልከቻቸው ጋር ቀጥሎ የተዘረዘሩ ማስረጃዎችን በማያያዝ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

 

  1. Curriculum vitae (CV)
  2. የትምህርት ደረጃን የሚገልጽ ሰርቲፊኬት አንድ ፎቶ ኮፒ
  3. የአካዳሚክ ማዕረግ የሚገልጽ ደብዳቤ
  4. በዩኒቨርሲቲ በመምህርነት ወይም በምርምር ተቋም በተመራማሪነት ያገለገሉበትን ጊዜ የሚገልጽ ደብዳቤ
  5. በዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉበትን ጊዜ የሚገልጽ ደብዳቤ
  6. በዩኒቨርሲቲው በአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንትነት ቢመደቡ የዘርፉን ሥራ ውጤታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል ስትራቴጂክ ዕቅድ በዝርዝር ማቅረብ የሚችል/ትችል የሆናችሁና

ፍላጎት ያላችሁ አመልካቾች ከኅዳር11/2013 እስከ ኅዳር 24/2013 ዓ.ም በሥራ ሰዓት ፕሬዝደንት ጽ/ቤት ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ቦርዱ ይገልጻል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ቦርድ

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት