በ2015 የትምህርት ዘመን አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቅበላ ቀን የካቲት 22/2015 ዓ/ም፣ የምዝገባ ቀን የካቲት 23 እና 24 ቀን 2015 ዓ.ም ፣ ትምህርት የሚጀመርበት ቀን የካቲት 27 ቀን 2015 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል፡፡

ስለሆነም ተማሪዎች በተጠቀሰው ቀን ወደ ዩኒቨርሲቲው በሚትመጡበት ጊዜ፡-

  • የ8ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ኦርጂናልና ሁለት የማይመለስ ኮፒ፣
  • ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኦርጂናልና ሁለት የማይመለስ ኮፒ፣
  • የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ኦርጂናልና ሁለት የማይመለስ ኮፒ፣
  • የፓስፖርት መጠን (Passport Size) የሆነ አራት ጉርድ ፎቶ፣
  • አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ፣ እንድሁም
  • ኮቪድ-19ን ለመከላከል የሚያስችል የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል

በመያዝ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ፣ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በጫሞ ካምፓስ በአካል ቀርባችሁ እንዲትመዘገቡ እያሳሰብን ስለምደባው ዝርዝር መረጃ ከዩኒቨርሰቲው ድህረ-ገጽ www.amu.edu.et ማግኘት የሚትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡

 ማሳሰቢያ፡- ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡

 የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት