Arba Minch University Renewable Energy Technology Research Center, Centre for Crop Health and Protection /CHAP/ and Satellite based Water Demand Estimation/SWaDE/ Technology Company has installed 3.3 KW Solar System to pump water for irrigation in Gamo Zone, Garda Marta Woreda, Bohe Kebele at Bazo River with the collaborative pilot project called "Optimizing Energy Demand in Rural Communities via Precision Agriculture Technology", on March, 01, 2024.Click here to see more photos.

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከ‹‹SNV-SEFFA›› ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ‹‹Sustainable Energy for Smallholder Farmers›› በሚል ርእስ ከአርባ ምንጭ፣ ሀዋሳ፣ ጅማ እና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች ከመጡ ተመራማሪዎች ጋር የካቲት 26/2016 ዓ/ም ወርከሾፕ አካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እንግሊዝ ሀገር ከሚገኙት ‹‹Centre for Crop Health and Protection /CHAP›› እና ‹‹SWaDE Technology Company›› ጋር በመተባበር በጋሞ ዞን ጋርዳ ማርታ ወረዳ ቦሄ ቀበሌ ባዞ ወንዝ ላይ ለመስኖ አገልግሎት የሚውል 3.3 ኪሎ ዋት ኃይል የሚያመነጭ በፀሐይ ኃይል የሚሠራ የኃይል ማመንጫ ተከላ አድርጓል፡፡ ተከላው ሦስቱ ተቋማት ‹‹Optimizing Energy Demand in Rural Communities via Precision Agriculture Technology›› በሚል ርእስ እያከናወኑ የሚገኙት የምርምርና ልማት ፕሮጀክት የሙከራ ሥራ ነው፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ከአሜሪካን ሀገር ኮሎራዶ ስቴት/Colorado State/ ዩኒቨርሲቲ የመጡት የግብርና ኤክስቴንሽን መ/ርና ተመራማሪ ፕ/ር አሰፋ ገብረአምላክ በማኅበረሰብ ጉድኝት፣ በዩኒቨርሲቲ-ኢንደስትሪ ትሰስር እንዲሁም በተዛማጅ ምርምሮች ዙሪያ ተሞክሮን ትኩረት ያደረገ ሥልጠና የካቲት 25/2016 ዓ/ም ለዩኒቨርሲቲው ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ሰጥተዋል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለ113 በሀገራችን ለ48 ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ‹‹ሴቶችን እናብቃ፤ ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ›› በሚል መሪ ቃል የካቲት 27/2016 ዓ/ም አክብሯል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ