The University of Leuven in Belgium, a leading research institution in Europe and a key partner in the AMU-IUC program, has contributed high-end ICT equipment, including High-Performance Computing (HPC) nodes, servers, switches, and access points valued at €2,229,766.85 to Arba Minch University. Click here to see more photos.

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሙያ ማበልጸጊያ ማዕከል ከ‹‹Derja.com›› እና ከ‹‹EthioJobs›› ጋር በመተባበር ለ2016 ዓ/ም የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂ ተመሪዎች ‹‹Dereja Academy Accelerator Program/DAAP/ ሥልጠና ከጥር 19 - መጋቢት 22/2016 ዓ/ም ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲ ኢንደስትሪ ትስስርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከጋሞ ዞን ቴክኒክና ሙያ መምሪያ ጋር በመተባበር ለቴክኒክና ሙያ ተቋማት መምህራን ‹‹Advance Solid Work››፣ ‹‹Basic Solid Work›› እና ‹‹ArchiCAD›› በተሰኙ ሶፍትዌሮች ዙሪያ ከመጋቢት 15-19/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ በሥልጠናው ከጋሞ፣ ጎፋ፣ ኮንሶና ደቡብ ኦሞ ዞኖች የተወጣጡ መምህራን ተሳትፈዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አሜሪካን ሀገር ከሚገኘው አላባስተር ኢንተርናሽናል/Alabaster International/ የተሰኘ ግብረ ሠናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ዶርዜ ሆሎኦና ሃይዞ ለተወጣጡ 18 ሴት ወጣቶችና እናቶች ከእንሰት ቃጫ እሴት የተጨመረባቸውና ቱሪስትን ማዕከል ያደረጉ ጌጣጌጦችንና ሌሎች ቁሳቁሶችን ማምረት የሚያስችል ሥልጠና ከመጋቢት 9/2016 ዓ/ም ጀምሮ ለ15 ቀናት ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡