የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሁሉ አቀፍ ሴክተር ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ለዩኒቨርሲቲው የግብርና ሳይንስ ኮሌጅ የአስተዳደር ዘርፍ ኃላፊዎች በአእምሮ ውቅር ዙሪያ ከመጋቢት 18-20/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

 Arba Minch University organized the 10th Annual National Research Symposium on Science for Sustainable Development on March 30, 2024. Click here to see more photos.

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ፣ ግብርና ሳይንስ እና ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጆች በመተባበር 10ውን ሳይንስ ለዘላቂ ልማት ዐውደ ጥናት መጋቢት 21/2016 ዓ/ም አካሂደዋል፡፡ በዐውደ ጥናቱ ከተለያዩ የሀገር ውስጥ ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ ተመራማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን 18 ጥናታዊ ጽሑፎችም ቀርበዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ከጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ጋር በመተባበር በጋሞ ዞን በሚገኙ የተመረጡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሳይንስ ቤተ ሙከራዎች ውስጥ ያሉ ኬሚካሎችንና ቁሳቁሶችን የመለየት፣ አስተማማኝ የሳይንስ ቤተ ሙከራዎችን አያያዝ መተግበርና መልሶ የማደራጀት ሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር መጋቢት 16/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡