የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥነ-ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ለቴክኖሎጂና ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ተመራቂ ተማሪዎች በሥነ-ምግባርና በሙስና ወንጀሎች ዙሪያ ሰኔ 20/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

አርባ ምንጭ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የ‹‹Ethio Jobs›› አጋር ድርጅት ከሆነው ‹‹Derja.com›› ጋር በመተባበር ለ2014 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች ‹‹Self Discovery››፣ ‹‹Building Self Image››፣ ‹‹Communication at the Work Place››፣ ‹‹Analytical Thinking››› በሚሉና ሌሎችም ርዕሶች ዙሪያ ከሰኔ 17-21/2014 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለጂኦግራፊና አካባቢያዊ ጥናት ት/ክፍል መምህር ዶ/ር አበራ ኡንቻ እና ለውሃ አቅርቦትና አካባቢ ምኅንድስና ፋከልቲ መምህር ዶ/ር አክበር ጩፎ የተባባሪ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን በቅድመ ምረቃ 193 እና በ2ኛ ዲግሪ 6 በድምሩ 199 ተማሪዎችን ሰኔ 26/2014 ዓ.ም አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 89ኙ ሴቶች ናቸው፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በ2ኛ ዲግሪ መርሃ ግብሮች በመደበኛ፣ በማታ፣ በክረምት፣ በሳምንት መጨረሻ እና በተከታታይና ርቀት፣ እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 2,561 ተማሪዎችን ሰኔ 25/2014 ዓ/ም አስመርቋል፡፡ ከተመራቂዎቹ መካከል 662ቱ ሴቶች ናቸው፡፡