አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኮንሶ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ጋር በመተባበር በሰብአዊ መብት አያያዝና አጠባበቅ እንዲሁም በሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ በኮንሶ ዞን ለሚገኙ 250 የፖሊስ አባላት ከየካቲት 6-9/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ክርስቲያን ኤይድ/Christian Aid/ እና ሶስ ሳህል /SOS Sahel Ethiopia/ ከተሰኙ ግብር ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ከተለያዩ ዞኖች ለተወጣጡ ማኅበራት ተወካዮችና ሥራ አጥ ወጣቶች ለ10 ቀናት የሚቆይ  የአሠልጣኞች ሥልጠና ከጥር 29/2016 ዓ/ም ጀምሮ እየሰጠ ይገኛል፡፡ ሥልጠናው የእንሰት ተረፈ ምርት ከሆነው ቃጫ ዕሴት የተጨመረባቸውና የተሻለ ዋጋ የሚያወጡ ጌጣጌጦችንና ሌሎች ቁሳቁሶችን ማምረት የሚያስችል ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሁሉ አቀፍ ሴክተር ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ለኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት መምህራንና አስተዳደር ሠራተኞች በአዕምሮ ውቅር ዙሪያ ከየካቲት 4-6/2016 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ አዘጋጅነት ከጥር 25/2016 ዓ/ም ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ የዋናው ግቢ ተማሪዎች የእርስ በእርስ እግር ኳስ ውድድር እየተካሄደ ነው፡፡ ውድድሩ በሁለት ምድብ በስድስት ቡድኖች መካከል የሚከናወን ሲሆን በ2016 ዓ/ም ለሚካሄደው የካምፓሶች ውድድር ዋናውን ግቢ የሚወክሉ ተጫዋቾችን ለመለየት ያለመ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በኢኮኖሚክስ ት/ክፍል በ‹‹Development Economics›› ትምህርት ፕሮግራም የ3 ዲግሪ ትምህርቱን ሲከታተል የቆየው ዕጩ ዶ/ር ሰሎሞን ከበደ የካቲት 01/2016 ዓ/ም የምርምር ሥራውን የውጪና የውስጥ ገምጋሚዎች እንዲሁም አማካሪዎች በተገኙበት አቅርቧል፡፡ የመመረቂያ ጽሑፉም አስፈላጊውን መስፈርት በማሟላት በአማካሪ ቦርዱ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡