AMU has hosted 2-day training on strategic issues linked with New Education Roadmap on the theme - ‘Sustain peaceful teaching-learning environment across university’ from 24th to 25th September, 2019, for entire university’s academic and administrative staff at Main Campus. Both freshmen and senior students were also oriented; while Sawla Campus imparted training to its community on October 1, 2019.Click here to see the pictures

በተለያዩ የውሃ ምህንድስና ዘርፍ በሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ለመማር አመልክታችሁ በተለያየ ምክንያት ፈተናው ያመለጣችሁ ተማሪዎች ለመጨረሻ ጊዜ ፈተናው  በቀን 28/01/2012 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የዩኒቨርሲቲው ቤተ-መጽሐፍትና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በአዲሱ የነጥብ ሥራ ምዘናና ደረጃ አወሳሰን (JEG) በሥሩ በተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተመደቡና ለነባር 170 ሠራተኞች የቤተ-መጽሐፍት ዓይነቶችና ምንነት፣ አደረጃጀት፣ ህግና ደንብ፣ አገልግሎት አሰጣጥ፣ ደንበኛ አያያዝ፣ የቴክኒክ ክፍሎች እንዲሁም ዲጂታላይዜሽንና አውቶሜሽን፣ ዶክዩሜንቴሽን እና ማጣቀሻ በሚሉ ርዕሶች ላይ ጳጉሜ 4-5/2011 ዓ/ም የሥራ ላይ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

የኢትዮጵያ ህዋ ሣይንስ ማኅበር የበላይ ጠባቂና የእንጦጦ ህዋ ምርምርና ልዩ ማሠልጠኛ ማዕከል የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ተፈራ ዋልዋ በጉጌ የህዋ ሣይንስ ምርምር ማዕከል ቅድመ አዋጭነት ጥናት ሂደት ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር መስከረም 16/2012 ዓ/ም ውይይት አካሂደዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ሲያካሂድ የነበረው የምርምር ማዕከሉ የቅድመ አዋጭነት ጥናት መጠናቀቁ በውይይቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው RUNRES ፕሮጀክት ስዊዘርላንድ ከሚገኘው ETH Zurich ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከመስከረም 13 - 14/ 2012 ዓ/ም ፕሮግራሙን ማስጀመሪያ የምክክር መድረክ በኃይሌ ሪዞርት አካሂዷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር ስምኦን ሽብሩ እንደገለፁት ፕሮጀክቱ በሙዝ እሴት ሰንሰለት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ ሲሆን ዓላማው ገጠርና ከተማን በምግብ እሴት ሰንሰለት በማገናኘት የአካባቢውን የምግብ ደኅንነትና ልማት ማሻሻልና መጠበቅ፣ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል እና በምግብ ራስን ለመቻል በሚደረጉ አገራዊ ጥረቶች ላይ የበኩሉንን ድርሻ መወጣት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ