የጫሞ ሐይቅ ዋነኛ ተፋሰስ በሆነው የኤልጎ ተፋሰስ ላይ የአፈር መሸርሸር መጠንን ለማወቅ ሲከናወን የነበረው የምርምር ፕሮጀክት ውጤት ይፋ ሆኗል፡፡ በጥናቱ መሠረት ከኤልጎ ተፋሰስ ብቻ በየዓመቱ 3.3 ሚሊየን ቶን ደለል አፈር እየተሸረሸረ ወደ ጫሞ ሐይቅ እንደሚገባ ተረጋግጧል፡፡ የደለል መጠኑ ሌሎች የሐይቁ ዋነኛ ተፋሰስ የሆኑትን ኩልፎና ሲሌ ተፋሰሶችን አያካትትም፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

የስነ-ትምህርትና ስነ-ባህርይ ሣይንስ ትምህርት ቤት በዩኒቨርሲቲው በ2012 ዓ/ም አዲስ ለተቀጠሩ 40 መምህራን ከኅዳር 1-5/2012 ዓ/ም ድረስ የማስተማር ክሂሎት ስልጠና ሰጥቷል፡፡

የትምህርት ቤቱ ዲን አቶ አንለይ ብርሃኑ እንደገለፁት የስልጠናው ዓላማ መምህራን ወደ ሥራው ዓለም በሚገቡበት ወቅት የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች ለመቅረፍ እንዲሁም አቅማቸው ጎልብቶ የመማር ማስተማሩን ሂደት በአግባቡ እንዲወጡ ለማድረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መምህራኑ ከስልጠናው በተጨማሪ አጋዥ መጽሐፎችን በማንበብና የተሻሉ ልምዶችን በመውሰድ የማስተማር ክሂሎታቸውን አዳብረው የተማሪዎችንና የራሳቸውን ውጤታማነት ለማረጋገጥ በሙሉ አቅም እንዲሠሩ አሳስበዋል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሐምሌ 3/2011 ዓ/ም ባካሄደው ውይይት ለደረጃው ካመለከቱ መምህራን መካከል መስፈርቱን ላሟሉ 3 ነባር መምህራን የተባባሪ ፕሮፈሰርነት ማዕረግ የሰጠ ሲሆን በተመሳሳይም ጥቅምት 20/2012 ዓ/ም በተደረገው ውይይት 4 ነባር መምህራን የተባባሪ ፕሮፈሰርነት ማዕረግ እንዲያገኙ ሴኔቱ ወስኗል፡፡

AMU today has held the kick-off meeting for ‘2nd International Field Course’ that involves 66 students from KU Leuven, Belgium, ETH Zurich, Switzerland and host AMU. Course will continue for two weeks in seven selected kebeles as research sites in Arba Minch Zuria i.e. Chano, Chencha, Mirab Abaya, Dorze, Lante, Geresse and Dembile. In all 22 resource persons will train students in respective areas. Click here to see the pictures

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከ ዓለም አቀፍ የውኃ አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር የሰዎችን ፍልሰት አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር የፕሮጀክት ማስተዋወቂያና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ጥቅምት 25/2012 ዓ/ም በኃይሌ ሪዞርት አዘጋጅቷል፡፡

የምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር ተሾመ ይርጉ የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልዕክታቸውን ሲያስተላልፉ አገራችን ኢትዮጵያ ከፍልሰት ጋር የተያያዙ በርካታ ችግሮችን እያስተናገደች የምትገኝ እንደመሆኗ ፕሮጀክቱ ለፖሊሲ አውጪዎች ሃሳቦችን በመጠቆም ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ