ዩኒቨርሲቲው 6ኛውን ዙር የሕክምና ዶክተሮችን ታኅሣሥ 11/2012 ዓ/ም በዋናው ግቢ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በደማቅ ሁኔታ ያስመርቃል፡፡

በዕለቱ 140 የሕክምና ዶክተሮችን የሚያስመርቅ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 37ቱ ሴቶች መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡ በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥና የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ይናገር ደሴ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና ተጋባዥ እንግዶች ይገኙበታል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

Institutional Enhancement Directorate Director, Dr Tesfaye Habtemariam, Principle Investigator of Grand Project - ‘Improving Quality of Teaching English Language through ICT tools,’ sharing progress of his ongoing endeavor, informed, in the 1st phase of survey, 30 teachers from three schools were found lacking ICT skills, that drove them to devise training for these individuals to acquire needed skills.

በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሲቪል ምኅንድስና ፋካልቲ በሥሩ ለሚገኙ መምህራንና ተማሪዎች ለኮንስትራክሸን ኢንዱስትሪ ጠቃሚ በሆኑ አዳዲስ ሶፍትዌሮች ዙሪያ ከጥቅምት 22 - ኅዳር 20/2012 ዓ/ም ለ5 ተከታታይ ቅዳሜ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ በሥልጠናው ላይ መምህራንን ጨምሮ ከ150 በላይ የቅድመ ምረቃና የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በወቅቱ ጉልህ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትና ሠልጣኞች የምስክር ወረቀት ተበርክቷል፡፡ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

31ኛውን ዓለም አቀፍ የኤች አይ ቪ/ኤድስ ቀን ምክንያት በማድረግ ‹‹ማኅበረሰቡ የለውጥ ኃይል ነዉ››፤ ‹‹ችግኞችን እንትከል፤ እንንከባከብ›› በሚል መሪ ቃል በአርባ ምጭ ከተማ ከኅብረት ለልማት ትማህርት ቤት እስከ አባያ ካምፓስ ድረስ ባለው አስፋልት መንገድ ግራና ቀኝ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ኅዳር 22/2012 ዓ.ም የችግኝ ተከላ አካሂዷል፡፡ ምስሉን ለማየት ከዚህ ይጫኑ

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን /ERA/ ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በአገሪቱ ውስጥ ከሚገኙ 7 ዩኒቨርሲቲዎች ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቶች ከተወጣጡ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በሲቪል ምህንድስና ሥር እየተሰጡ ባሉ የ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች አፈፃፀም ሂደት ላይ ኅዳር 19/2012 ዓ/ም በኃይሌ ሪዞርት ውይይት አካሂዷል፡፡Click here to see the pictures