የዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ ከጂኦግራፊና አካባቢ ጥናት ትምህርት ክፍል ጋር በመሆን ዓለም አቀፉን የጂ አይ ኤስ ቀን ‹‹Progressing GIS›› በሚል መሪ ቃል ኅዳር 9/2013 ዓ/ም በፓናል ውይይት አክብሯል፡፡

ማክሰኞ ኅዳር 08/2013 ዓ/ም ከቀኑ 5:30 ጀምሮ “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” በሚል መሪ ቃል በአገር ደረጃ እንዲካሄድ ለቀረበው አገራዊ ጥሪ መላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ በየካምፓሱና በያለበት በመቆም ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ያለውን አጋርነት በተግባር አረጋግጧል፡፡

2ኛ ዙር የደምባ ተፋሰስ አፈር መሸርሸር ቅነሳና የሸክላ ሠሪዎችን ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ማሻሻል ላይ ያተኮረ የምርምር ፕሮጀክት አጀማመር ውይይት በጋሞ ዞን ዲታ ወረዳ ጥቅምት 21/2013 ዓ.ም ተካሂዷል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው ኬሚስትሪ ቤተ-ሙከራ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚረዱ የንጽህና መጠበቂያዎች አመራረት ሂደትን አስመልክቶ ጥቅምት 24/2013 ዓ/ም ጉብኝት አካሂደዋል፡፡

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መመሪያ መሠረት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአማካሪ ምክር ቤት ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ተቋቁሟል፡፡