የዩኒቨርሲቲው የባህልና ቋንቋ ጥናት ተቋም በተቋሙ ተመራማሪዎች፣ በማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ መምህራንና በድኅረ ምረቃ ተማሪዎች የቀረቡ የምርምር ንደፈ ሃሳቦችን ሚያዝያ 15/2013 ዓ/ም ገምግሟል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው የምርምር ዳይሬክቶሬት 7ኛውን ሀገር አቀፍ ምርምር ለልማት ጉባዔ ከሚያዝያ 29-30/ 2013 ዓ/ም አካሂዷል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ የምርምር ጽሑፎች በመሰል አውደ ጥናቶች እየቀረቡ መተቸታቸው የምርምር ግኝቶችን የሚያዳብር ሲሆን ተመራማሪዎችና መምህራን ሳይንሳዊ ግኝቶችን እንዲለዋወጡና የምርምር ጽሑፎቻቸውም ለማኅበረሰቡ ችግር መፍትሔ እንዲጠቁሙ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የዩኒቨርሲቲው የማኅበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብ ኮሌጅ የሶሾሎጂ እና ሶሻል አንትሮፖሎጂ ትምህርት ክፍል ቤልጂየም፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሞዛምቢክ፣ ዝምባብዌ ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች የሶሻል አንትሮፖሎጂ ትምህርት ክፍሎች ጋር በመተባበር ከሚያዝያ 4 - 13/2013 ዓ/ም ድረስ ለተከታታይ 10 ቀናት የመስክ ትምህርት /Field School/ ፕሮግራም አካሂዷል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ኢሳት ቴሌቪዥን ከመጋቢት 20/2013 ዓ/ም ጀምሮ “ጎልጉል” በተሰኘ ፕሮግራሙ ለተከታታይ አራት ሳምንታት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን ገጽታ በከፍተኛ ሁኔታ ሊያጎድፍ የሚችል መረጃ ማሰራጨቱ ይታወሳል፡፡ የቴሌቪዥን ጣቢያው ከሚዲያና ከጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር ውጪ ዓላማውና ተልዕኮው ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ ወቅታዊ ያልሆነና በተጨባጭም ለአሁናዊው ተቋማዊና አገራዊ ሁኔታ የማይመጥን፣ ለዩኒቨርሲቲውና ለአካባቢው ማኅበረሰብ፣ ለዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ምሩቃን እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው ወዳጆችና ደጋፊዎች ሁሉ አሳዛኝ የሆነና የተጋነነ ፕሮግራም አሰራጭቷል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ ሚዲያው ወገንተኛ፣ ብይን ሰጭና ፈራጅ የነበረ በመሆኑ እንዲሁም አንዳንድ የዩኒቨርሲቲው የቀድሞና የአሁን ኃላፊዎች የሰጡት አስተያየት ብዥታ የፈጠረ ስለሆነ በጉዳዩ ላይ ሚዛናዊና ወቅታዊ መረጃ መስጠት አስፈልጓል፡፡

በኢንተርንሺኘ ላይ ያላችሁ የአውቴኢ እና የአምቴኢ ተማሪዎች በሙሉ

  • የሃይድሮሊክና ውሃ ሀብት ምኅንድስና ፋከልቲ
  • የውሃ ሀብትና መስኖ ምኅንድስና ፋከልቲ
  • የውሃ አቅርቦትና አከባቢያዊ ምኅንድስና ፋከልቲ