- Details
በ2012 ዓ/ም ሊሰጥ የነበረው ሀገር አቀፍ የሕግ መውጫ ፈተና (Exit Exam) በኮቪድ-19 መከሰት ምክንያት ወደ 2013 ዓ/ም መተላለፉ ይታወሳል፡፡
ስለሆነም ፈተናው የሚሰጠው ከኅዳር 1-4/2013 ዓ/ም በመሆኑ ፈተናውን መውሰድ የምትፈልጉ በሙሉ ከጥቅምት 2-12/2013 ዓ/ም ድረስ ብቻ ብር 664.00 ( ስድስት መቶ ስልሳ አራት ብር ብቻ) በኤጀንሲው የባንክ ሒሳብ ቁጥር 0171597578400 ገቢ ያደረገባችሁበትን ደረሰኝ በመያዝ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ት/ቤት ቀርባችሁ መመዝገብ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡
Read more: በ2013 ዓ/ም የሕግ መውጫ ፈተና (Exit Exam) መፈተን ለምትፈልጉ በሙሉ
- Details
ለድህረ ምረቃ አዲስ አመልካቾች በሙሉ
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ት/ቤት ለ2013 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በመደበኛ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን እየመዘገባ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
መስከረም 30 ዕለተ ቅዳሜ 2013 ዓ/ም ሊሰጥ የነበረው የድኅረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና ፈተናው የሥራ ቀናት ላይ እንዲሆን ከተለያዩ አመልካቾች ጥያቄ በቀረበው መሠረትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ምክንያት ፈተናው ለ3ኛ ጊዜ ለጥቅምት 09 ዕለተ ሰኞ 2013 ዓ/ም የተዛወረ መሆኑን ከይቅርታ ጋር እንገልፃለን፡፡
- Details
የዩኒቨርሲቲው ካውንስል መስከረም 20/2013 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የ2013 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ ላይ ውይይት በማድረግ አፅድቋል፡፡ ለዕቅዱ ማስፈጸሚያ ለመደበኛ እና ለካፒታል በድምሩ ብር 1,594,367,000 ተመድቧል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
ለድህረ ምረቃ አዲስ አመልካቾች በሙሉ
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ድህረ ምረቃ ት/ቤት ለ2013 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በመደበኛ እና በሳምንት መጨረሻ መርሃ ግብር መስፈርቱን የሚያሟሉ አዲስ አመልካቾችን እየመዘገባ መቆየቱ ይታወቃል፡፡
ትናንት በወጣው የፈተና ጊዜ ማስታወቂያ በ25/01/13 ዓ/ም ሊሰጥ የነበረው የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና በአመልካቾች ጥያቄ መሠረት ለ30/01/13 ዓ/ም የተዛወረ መሆኑን እየገለፅን ተፈታኞች በተጠቀሰው ቀን ከጥዋቱ 02፡30 ጀምሮ በየተመደባችሁበት የመፈተኛ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡