- Details
ለአርባ ምንጭ ዩነቨርሲቲ የ2012 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ
ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ተግባቦት አማራጮች ተመራቂ ተማሪዎች ጥቅምት 25 እና 26 ግቢ እንድትገቡ ከጥቅምት 03/2013 ዓ/ም ጀምሮ ያስተዋወቀ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ በተፈጠረው አሁናዊ አገራዊ ሁኔታ ምክንያት ከተለያዩ አከባቢዎች የትራንስፖርት አገልግሎት ችግር የተፈጠረ መሆኑን መገንዘብ ችለናል፡፡
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የኢትዮጵያ ጂኦ ስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲትዩት በጂኦ ስፓሻል ትምህርትና ሥልጠና፣ ምርምር፣ ዕድገት እንዲሁም መረጃ ልውውጥ ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የኢትዮጵያ ጂኦ ስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ለዘርፉ ዕድገት በጋራ ለመሥራት ተስማሙ
- Details
ዩኒቨርሲቲው ለ7 ወራት በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን የቅድመ ምረቃ ትምህርት ለማስጀመር በመማር ማስተማሩ ዘርፍ አስፋላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ገልፀዋል፡፡
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በኮቪድ-19 ምክንያት የተቋረጠውን የመማር ማስተማር ሥራ ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለፀ
- Details
ላለፉት ሦስት ዓመታት እየጣለ ባለው ዝናብ አማካኝነት እየገባ ባለው ከፍተኛ ደለል ምክንያት የዓባያና ጫሞ ሐይቆች ከመጠን በላይ መሙላታቸውና ከብዙ ዓመታት በኋላ ሐይቆቹ ዳግም መገናኘታቸው ተገልጿል፡፡ ላለፉት 45 ዓመታት ተቋርጦ የቆየው ጫሞ በሰገን በኩል የሚያደርገው ፍሰትም ጥቅምት 16/2013 ዓ/ም ዳግም ጀምሯል፡፡
Read more: የዓባያና ጫሞ ሐይቆች ከመጠን በላይ በመሙላት ከብዙ ዓመታት በኋላ ዳግም መገኛኘታቸው ተገለጸ
- Details
የ2013 የትምህርት ዘመን፡-
1. የምዝገባ ቀናት - ከጥቅምት 18-20/2013 ዓ.ም
2. የምዝገባ ቦታ - በካምፓስ ሬጅስትራር ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች
3. ትምህርት የሚጀመርበት ቀን ጥቅምት 23/2013 ዓ.ም መሆኑን እንገልጻለን፡፡
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት