ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራንና ተመራማሪዎች የ2030 የምርምር ትኩረት ዓለም አቀፍ የፕሮጀክት አጻጻፍን አስመልክቶ ከታኅሣሥ 22-24/2016 ዓ/ም ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ ሥልጠናው ዓለም አቀፍ የፕሮጀክት አጻጻፍ ስልቶች ምንነት፣ የፕሮጀክት አጻጻፍ ሂደትን መገምገም፣ የእድገት ጽንሰ ሃሳብ እንዲሁም ዘላቂ የልማት ግቦች አተገባበር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ እየተከናወኑ የሚገኙ የከተማ ግብርና ሥራዎችን ታኅሣሥ 15/2016 ዓ/ም ጎብኝተዋል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት በ2016 የትምህርት ዘመን ወደ ዩኒቨርሲቲው ለመጡ አዲስ ገቢ ሴት ተማሪዎች ከታኅሣሥ 04-5/2016 ዓ/ም የሕይወት ክሂሎት ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ሚኒስቴር ሱፐርቪዥን ቡድን ለዩኒቨርሲቲው በሰጠው ግብረ መልስና በሌሎች ተያያዥ ተቋማዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ጋር ከታኅሣሥ 04-11/2016 ዓ/ም በሁሉም ካምፓሶች ከመምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

ወ/ሮ ታየች በለጠ ከአባታቸው አቶ በለጠ ማሞ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ጂንጌ አጉርሽ በቀድሞው ጋሞ ጎፋ ክፍለ ሀገር አርባ ምንጭ ከተማ መስከረም 20/1965 ዓ/ም ተወለዱ፡፡