የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የቤተ-መጻሕፍትና መረጃ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የ"Anti-Plagiarism Software and Subscribed Journals" ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ግንቦት 15/2015 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ፈረንሳይ ሀገር ከሚገኝ "Fund for Innovative Development (FID)" ድርጅት ጋር በመተባበር "Adoption of Rhizobium Inoculant Technology (ARIT)" የተሰኘ የትብብር ፕሮጀክት የተፈጥሮ ማዳበሪያ "Bio-Fertilizer" ማምረት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሠራ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

ወ/ሮ ድርሻዬ አድማሱ አላሆ ከአባታቸው አቶ አድማሱ አላሆ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ትርፍነሽ ሞገስ በአርባ ምንጭ ከተማ ታኅሣሥ 24/1984 ዓ/ም ተወለዱ፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት የማኅበረሰብ ጉድኝት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከጋሞ ዞን ፍትሕ መምሪያ ጋር በመተባበር በዞኑ ከሚገኙ ሦስት የከተማ አስተዳደሮችና አራት ወረዳዎች ዐቃቤያን ሕጎች፣ ወንጀል መርማሪ ፖሊሶች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በወንጀል በተጠረጠሩ፣ በተያዙ እና በተከሰሱ ሰዎች መብቶች ዙሪያ ግንቦት 12/2015 ዓ/ም ውይይት አካሂዷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ላይ በደረሰው ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ መምህራን የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን በመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ስም ይገልጻል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ለመምህራኑ ቤተሰቦች፣ ዘመዶችና የሥራ ባልደረቦች እንዲሁም ለመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ መጽናናትን ይመኛል፡፡