የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማኅብረሰብ ጉድኝት ም/ፕሬዝደንት ጽ/ቤት በምርምር ትብብር ፕሮጀክቶች ችግሮችና ዕድሎች ዙሪያ ሐምሌ 13/2016 ምክክር አካሂዷል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ የኢኮኖሚክስ ትምህርት መስክ 4 ዓመት የሳምንት መጨረሻ ተማሪ የነበረው ተማሪ ዋና ሳጅን መለሰ አባይነህ ከቡልቂ ወደ አደጋው ቦታ ተጎጂዎችን ለመርዳት በሄደበት አደጋው በድጋሚ በመከሰቱ በድንገት ሕይወቱ ያለፈ በመሆኑ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዞመዶቹና ጓደኞቹ እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው በተለይ ለሳውላ ካምፓስ ማኅበረሰብ መጽናናትን ይመኛል።

 አቶ ነጋልኝ ስለሺ ከአባታቸው ከአቶ ስለሺ ስሜ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብሩክነሽ ብርሃኑ ሚያዝያ 08/1987 ዓ.ም በገዜ ጎፋ ወረዳ ቡልቂ ከተማ ተወለዱ፡፡ 

በፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ለተባባሪ አሠልጣኝነት በወጣው ማስታወቂያ መሠረት በተወሰነው ጊዜ በኮሚሽኑ ኢ-ሜይል መረጃችሁን የላካችሁ አመልካቾች የላካችሁትን መረጃ ኮፒ /Hard Copy/ እስከ 18/11/2016 ዓ.ም ድረስ በዋናው ግቢ የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ቢሮ እንድታቃርቡ እንገልጻለን፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ትናንት ረፋድ አካባቢ በተከሰተው የመሬት ናዳ አደጋ ምክንያት በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ በደረሰው ከፍተኛ ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን በዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ስም እየገለጸ ለኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ፣ ለዞኑና ለክልሉ ማኅበረሰብ መጽናናትን ይመኛል።