- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ“SIFA/Skills Initiative for Africa-Funding Window III” በሙከራ የተረጋገጡ የእንሰት ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለሴቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር በቀረጸው ፕሮጀክት አሸናፊ በመሆን ከአፍሪካ ኅብረት የልማት ኤጀንሲ(African Union Development Agency/AUDA-NEPAD) ጋር ነሐሴ 15/2016 ዓ/ም በአዲስ አበባ አፍሪካ ኅብረት አዳራሽ የጋራ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱን ተቋሞቻቸውን ወክለው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝደንት ተባባሪ ፕ/ር በኃይሉ መርደኪዮስ እና የኔፓድ “NEPAD” ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሪት ናርዶስ በቀለ ተፈራርመዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የማስተማሪያ እና ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በቅርቡ ተመርቆ በተወሰኑ የሕክምና ዘርፎች በይፋ ሥራ መጀመሩ ይታወሳል፡፡ ሆስፒታሉ ቀደም ብሎ እየሰጠ ካለው የሕክምና አገልግሎቶች በተጨማሪ ከዛሬ ነሐሴ 10/2016 ዓ/ም ጀምሮ የጥርስ፣ የኤም.አር.አይ/MRI Machine/ እና የሥነ ደዌ/Pathology/ የሕክምናና ምርመራ አገልግሎችን ያስጀመረ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሙያ ማበልጸጊያ ማዕክል ከደረጃ ዶት ኮም/Dereja.com/ እና ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ከጋሞ ዞን የተለያዩ ወረዳዎችና ከአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር በ2015/16 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው በዞኑ ሥራ ዕድል ፈጠራና ልማት ኢንተርፕራይዝ ቢሮ ለተመዘገቡ ከ270 በላይ ሥራ ፈላጊ ወጣቶች ከነሐሴ 3/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ወራት የሚቆይ የ"Deraja Academy Accelerator Program (DAAP)" ሰዋዊና ሙያዊ ክሂሎት ሥልጠና እየሰጠ ነው፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: ዩኒቨርሲቲው ለሥራ ፈላጊ ወጣቶች በሰዋዊና ሙያዊ ክሂሎት ዙሪያ ሥልጠና እየሰጠ ነው
- Details
በዛሬው ፈጣን ዓለም ባላሰለሰ ትምህርት እና የክሂሎት ዕድገት ውስጥ መሳተፍ ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ እጅግ አስፈላጊነቱ ግልጽ ሲሆን በዕረፍት ላይ ላላችሁ ተማሪዎች፣ ለወጣት ባለሞያዎች፣ ራሳቸሁን በዕውቀት በመገንባት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር በጎ ተፅዕኖ ለመፍጠር ለምትጓጉ ሁሉ የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ፕሮጀክት ቀዳሚ ሊያደርጋችሁ ተሰናድቶላችኋል። የትምህርት እና የዕውቀት መነሻችሁ እና ያላችሁበት ደረጃ ምንም ይሁን ያላችሁን ክሂሎት ለማሳደግም ሆነ አዲስ ነገር ለማወቅ ለምትሹ ሁሉ ሰፊ የእድል በር ተከፍቶላችኋል። በመላው ኢትዮጵያ ያላችሁ የክሂሎት አበልፃጊዎች፣ አሳዳጊዎች፣ ዩኒቨርሲቲዎች ይህንን ፕሮጀክት እና እንቅስቃሴዎቹን የሚደግፉ ይሆናል።
ውድ ባለተሰጥዖዎች፣ የኢትዮጵያችን ጥንካሬ በእናንተ እድገት ላይ የተመሠረተ ነው። ለመመዝገብ: http://www.ethiocoders.et
- Details
Background
This PhD supervision training is initiated by the Ethiopian SuperStars project. The Ethiopian Superstars is an international training program that involves 7 Ethiopian universities (Addis Ababa University, Ambo University, Arba Minch University, Bahir Dar University, Hawassa University, Jimma University and Mekelle University). The project is coordinated by Jimma University and Ghent University, is financially supported by VLIR-UOS (www.vliruos.be) and runs from September 2023 to August 2026. The overall vison of Ethiopian SuperStars project is strengthening the advisory and coaching skills of academic staff at Ethiopian higher education institutions. To realize this, Ethiopian SuperStars works towards the following four milestones:
Read more: A Call for PhD SUPERVISION Training Applicants - 2024