የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የደቡብ ሱዳን ሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በጋምቤላ ክልል ኑዌር እና አኝዋክ ዞኖች በሚገኙ 13 ቀበሌያት ንፁሃን ዜጎቻችን ላይ የፈፀሙትን አሰቃቂ ግድያና ዝርፍያ በማውገዝ ሚያዝያ 17/2008 ዓ/ም የህሊና ፀሎትና የጧፍ ማብራት ሥነ-ሥርዓት አከናውኗል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

‹‹ትውፊታዊ ዕውቀት፣ የባህል ብዝሃነትና ቅርስ አስተዳደር በኢትዮጵያ›› አራተኛው ሀገራዊ አውደ ጥናት ሰኔ 14/2008 ዓ/ም በማህበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብ ኮሌጅ አዘጋጅነት ተከናውኗል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በ2008 የትምህርት ዘመን አንደኛ መንፈቀ ዓመት የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የሽልማት ፕሮግራም በሁሉም ካምፓሶች ተካሄደ፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በጋሞ ጎፋ ዞን ለቦንኬ ወረዳ 1ኛ ደረጃ የመጀመሪያ ሳይክል ት/ቤቶች መምህራን የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ከመጋቢት 10/2008 ዓ/ም ጀምሮ ለአስር ተከታታይ ቀናት ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የ2008 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የቅድመ-ምረቃ ምሽት ፕሮግራም ሰኔ 16/2008 ዓ.ም በዋናው ግቢ ስታዲየም በልዩ ድምቀት ተከናውኗል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡