As Ethiopia begins to rejoice in Growth and Transformation Plan-I success and started rallying its might for GTP-II to bolster economy, Arba Minch University too, has began to relook into the laid-out benchmarks supposed to narrow the gap between GTP-II goals and present-day reality.

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሣውላ ካምፓስ ለመጀመሪያ ጊዜ በ'Adult Education & Community development'፣ 'Communication & Media Studies'፣ 'Logistics & Supply Chain Management' እና 'Finance & Economic Development' 191 ተማሪዎችን ተቀብሎ ህዳር 19/2008 ዓ.ም ማስተማር ጀምሯል፡፡

College of Natural Sciences’ department of Meteorology and Hydrology along with Ethiopian Meteorological Society (EtMS) in a daylong symposium discussed vital climatic issues impacting Ethiopian climate in the globe and possible mitigation strategies. Click here to see the pictures.

Arba Minch University in association with the House of Federation and Ministry of Education will celebrate 10th Ethiopian Nations, Nationalities and People’s Day with great enthusiasm on 26th November, 2015, at Main Campus. 

ዩኒቨርሲቲው በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ እየሰራ መሆኑን የአከዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚደንት ቢሮ እና የሥርዓተ-ፆታ ዳይሬክቶሬት ገልፀዋል፡፡

በትምህርት ተቋማትና በሴክተር መስሪያ ቤቶች አመራር የሴቶችን ተሳትፎ ለማሳደግ መንግስት በያዘው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ መሰረት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 7 % የነበረውን የሴት መምህራን ቁጥር በ5 ዓመት ውስጥ ወደ 36% ለማሳደግ ዕቅድ ይዟል ፡፡በዚህም መሰረት በዩኒቨርሲቲው ሴኔት ውሳኔ በ2007 /ም ከየትምህርት ክፍሉ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የተመረቁ 34 ሴት ተማሪዎችን በዩኒቨርሲቲው በመምህርነት በመቅጠር ዕቅዱን ለማሳካት እየሠራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ደርዛ ገልፀዋል ፡፡

የዩኒቨርሲቲው የስርዓተ ፆታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሪት ሙኒት መኩሪያ በበኩላቸው መምህራኑ በቅድሚያ የህይወት ክህሎት ፣ የጥናትና ምርምር ስነ-ዘዴ፣ የስርዓተ ፆታ ምንነትና ፅንሰ ሃሳብ ስልጠና እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል ፡፡ እንደ ዳይሬክተሯ ገለፃ በርካታ ሴት መምህራንን መቅጠር የተፈለገው በዩኒቨርሲቲው በመምህርነትና በአመራር ላይ በቂ ሴቶች ባለመኖራቸውና በቀጣይም የሴቶችን የውሳኔ ሰጪነት ሚና ለማሳደግ ብሎም ሴት ተማሪዎችን እንዲያበረታቱ ለማድረግ ነው ፡፡በመሆኑም አዲስ ተቀጣሪ መምህራን ጠንክረው እንዲሰሩና ለሌሎችም ተምሳሌት እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡