• SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • AMU
    • About AMU
    • Presidents Message
    • Campus Guide
    • Contact us
  • Administration
    • Presidents' Office
      • AMU President
      • Academic Affairs
      • Research and Community Service
      • Administration
  • Directorates
  • Academics
    • School of Graduate Studies
    • Institutes
      • Arba Minch Institute of Technology
      • Arba Minch Water Technology
    • Colleges
      • Agriculture
      • Business & Economics
      • Medicine and Health Sciences
      • Natural & Computational Sciences
      • Social Sciences & Humanities
      • Continuing & Distance Education
      • Sawla Campus
    • Schools
      • School of Law
      • School of Pedagogical and Behavioral Sciences
      • School of Medicine
    • Sport Academy
  • Research
  • Registrar
    • About Us
    • Alumni Registration
    • Alumni
  • Partnership
    • Our Partners
      • International Partners
      • Local Partners
    • Ongoing Projects
    • Completed Projectss
      • Recently Completed
      • Past Projects
    • GCPM Online Forms
  • Journals
    • OMOIJS Journal
    • EJBSS Journal
    • EJWST Journal
    • AMUJCLS Journal
    • EIJET journal
  • Symposia
    • Enset Symposium
    • Enset Symposium 2024
newyearjpg-2017-3.jpeg
1Renaissance_week_Celebration.jpeg
previous arrow
next arrow

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት 39ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

Details
Wed, 02 September 2020 9:27 am

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት 39ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ከነሐሴ 21-23/2012 ዓ/ም ድረስ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለ3 ቀናት ተካሂዷል፡፡

መርሃ-ግብሩን በአገር ባህልና ወግ መሠረት መርቀው የከፈቱት የጋሞ አባቶች ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲዎች ሀገርንና ዓለምን የሚለውጡ አዳዲስ ሐሳቦችና ፈጠራዎች የሚፈልቁበት ቦታ እንጂ ተማሪዎች በቋንቋ፣ በብሄርና በሐይማኖት እየተከፋፈሉ የሚጣሉበት ሥፍራ እንዳይሆንና በተቋማቱ ከዚህ ቀደም እየታዩ የነበሩ የሠላም መደፍረሶች እንዳይከሰቱ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች፣ የተማሪዎች ኅብረትና ሌሎችም የሚመለከታቸው ሁሉ አካላት ለሠላም ዘብ በመቆም የአገራችን ብልፅግና እንዲረጋገጥ በትኩረት እንዲሠሩ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከትምህርት ሚኒስቴር ለተገኙ ተወካዮች በባህሉ መሠረት ጥብቅ አደራ ከእርጥብ ሣር ጋር በመስጠት ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ የብሄር ማንነታችን የሚያብበው እንደ ሀገር ኢትዮጵያ ስትኖር ነው ያሉት አባቶቹ ሁላችንም ኢትዮጵያ በምትባል ምድር ላይ የተዘራን የሰብል ዓይነቶች በመሆናችን የሀገራችንን ህልውና ልናስጠብቅ እንደሚገባ በአጽንዖት ተናግረዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Read more: የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ኅብረት 39ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በማቴሪያል ፊዚክስ የዶክትሬት ዲግሪ ፕሮግራም ሊከፍት ነው

Details
Fri, 28 August 2020 1:30 pm

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የፊዚክስ ትምህርት ክፍል በማቴሪያል ፊዚክስ የዶክትሬት ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራም ለመክፈት የውጭ ሥርዓተ ትምህርት ነሐሴ 18/2012 ዓ/ም ግምገማ አካሂዷል፡፡

የአካዳሚክ ጉ/ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ትውልድና የምርምር ዩኒቨርሲቲ እንደመሆኑ የ2ኛና 3ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞችን በማስፋፋትና በጥራት መስጠት ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሠራ የቆየ ሲሆን በፊዚክስ ትምህርት መስክ የሚከፈተው የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራምም የዚሁ ሥራ አካል ነው ብለዋል፡፡ አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች ሲከፈቱ የሥርዓተ-ትምህርቱ ዝግጅት በርካታ ሂደቶችን እንደሚያልፍ የገለፁት ዶ/ር የቻለ ፕሮግራሞችን መክፈት በራሱ ግብ ባለመሆኑ ሥርዓተ-ትምህርቱን በየጊዜው የመከለስ እንዲሁም ትምህርቱን በጥራት መስጠትና ምርምር ተኮር የማድረግ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ በመሆኑ በቀጣይነት ይሠራል ብለዋል፡፡  ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በማቴሪያል ፊዚክስ የዶክትሬት ዲግሪ ፕሮግራም ሊከፍት ነው

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እያስገነባ የሚገኘውን የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል በ2013 በጀት ዓመት ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ

Details
Fri, 28 August 2020 1:20 pm

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እያስገነባ የሚገኘውን የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታን በ2013 በጀት ዓመት በከፊል ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የሆስፒታሉን የግንባታ ሂደት ነሐሴ 15/2012 ዓ/ም በጎበኙበት ወቅት ተገልጿል፡፡

በ2007 ዓ/ም የተጀመረው የሆስፒታሉ ግንባታ በዲዛይን ማስተካከያና ተጨማሪ ግንባታ፣ በሆስፒታሉ ግንባታ ቦታ ተነሺዎች፣ የክፍያዎች መዘገየት፣ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ የዋጋ ንረት፣ በግንባታ አካባቢ የሚገኙ የመብራት፣ የውሃና የስልክ መስመሮች እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች ይጠናቀቃል ከተባለበት ጊዜ የዘገየ ሲሆን እስካሁን ባለው ሂደት 77 በመቶ የግንባታ ሂደት መጠናቀቁ በጉብኝቱ ወቅት ተጠቅሷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ እያስገነባ የሚገኘውን የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል በ2013 በጀት ዓመት ሥራ ለማስጀመር እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች የዩኒቨርሲቲውን የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዞችን ጎበኙ

Details
Fri, 28 August 2020 1:01 pm

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው የሚገኙ የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዞችን ሐምሌ 20/2012 ዓ/ም ጉብኝተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ቢዝነስና ልማት ም/ፕሬዝደንት ወ/ሮ ታሪኳ ወ/መድኅን ጉብኝቱ በዩኒቨርሲቲው ያሉ የተለያዩ የገቢ ማመንጫ ተቋማት ያሉበትን የአፈፃፀም ደረጃና ችግሮች በአካል በማየት ለቀጣይ ሥራዎች አቅጣጫና ውሳኔ ለመስጠት የሚረዱ ሀሳቦች ለማግኘት የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የራሳቸውን ገቢ በማመንጨት ወጪያቸውን በከፊል እንዲሸፍኑ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በ2007 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው የእንጨትና ብረታ ብረት፣ የሕትመትና የግብርና ኢንተርፕራይዞች ተመስርተው ሲሰሩ መቆየታቸውን ያስታወሱት ም/ፕሬዝደንቷ መሰል ጉብኝቶች መደረጋቸው የዘርፉን ወጤታማነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ናቸው ብለዋል፡፡ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ

Read more: የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች የዩኒቨርሲቲውን የገቢ ማመንጫ ኢንተርፕራይዞችን ጎበኙ

Dr Eliezer Manus: Kindness and humility personified

Details
Thu, 20 August 2020 2:49 pm

A Philippine expatriate, Dr Eliezer B Manus, 65, who worked with Arba Minch University for over 13 years in Architecture & Urban Planning Department, died of prolonged illness, was buried in Manila, Philippine. He is survived by wife Prof Madelyn Manus and only son Mr Michael Manus, a lecturer in AMU.

Dr Eliezer had started his employment with AMU on 9th October, 2007, till he left for his country in August 2020 for treatment to his ailment and soon after reaching his nation he died. Click here to see the pictures

Read more: Dr Eliezer Manus: Kindness and humility personified

  1. Call for papers
  2. Advertisement
  3. ማስታወቂያ
  4. Dr Addisu Fekadu wins Josef G Knoll European Science Award 2020

Page 333 of 528

  • 328
  • 329
  • 330
  • 331
  • 332
  • 333
  • 334
  • 335
  • 336
  • 337

Downloads

  • Newsletter
  • Registrar
  • Academic Calendar
  • Finance & Budget Transparency

Quick Links

  • News
  • Vacancies
  • AMU Intranet
  • ICT Center

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning
  • Facebook
  • X
  • Telegram
  • Youtube
  • Email

Contact us

Corporate Communication
P.O. Box 21
Arba Minch University

Tel: +251-46881-4986
Fax: +251-46881-0820/0279
E-mail: corcom@amu.edu.et , ictc@amu.edu.et

Registrar

  • About Us
  • Alumni
  • Alumni Registration
  • Contact us

Colleges

  • Agriculture
  • Business & Economics
  • Medicine and Health Sciences
  • Natural Sciences
  • Social Sciences & Humanities

Systems

  • SMIS
  • AMU Mail
  • Digital Library
  • AMU RDB
  • E-learning

Copyright © 2025 Arba Minch University. 

  • Campus Guide
  • Contact Us
  • Sitemap