የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የመምህራንን የምርምር አቅም የሚያጎለብትና የምርምር ሥራ ጥራትን የሚያሳድግ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ከመጋቢት 21 - 24/2008 ዓ/ም ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የማህበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤትና በህክምና ላብራቶሪ ትምህርት ክፍል አዘጋጅነት የወባ በሽታ የቤተ-ሙከራ ምርመራ ውጤት ጥራትን ለማስጠበቅ ከመጋቢት 12-15 /2008 ዓ/ም ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በህክምና ዶክትሬት 47 እንዲሁም በስነ ህንጻና ከተማ ፕላን 57 በድምሩ 104 ተማሪዎች የካቲት 26/2008 ዓ.ም አስመርቋል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ከደቡብ ኦሞ፣ ከሰገን አካባቢ ህዝቦች፣ ከወላይታና ከዳውሮ ዞኖች ለተወጣጡ ከ60 በላይ የጤና ጣቢያና የሆስፒታል ባለሙያዎች የስጋ ደዌ፣ የቲቢና የኤች አይ ቪ/ኤድስ በሽታዎችን ለመከላከል የሚያስችል ስልጠና ከየካቲት 27 - መጋቢት 10 /2008 ዓ/ም ለአስር ቀናት በሁለት ዙር ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከኢትዮጵያ የአካባቢና ደን ምርምር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር  ለመድኃኒትነት አገልግሎት በሚውሉ ሀገር በቀል ዕጽዋትና በሞሪንጋ /ሽፈራው/ ተክል ዙሪያ ሀገር አቀፍ ሲምፖዚዬም አካሂዷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡ Click here to see the News Video.