/ ስምዖን ሽብሩ ከአባታቸው አቶ ሽብሩ ጨጨ እና ከእናታቸው / አምኔ ጎሌ በቀደሞው ጋሞ አውራጃ በኦቾሎ ቀበሌ ግንቦት 29/1960 / ተወለዱ፡፡ / ስምዖን የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በላንቴ 1 ደረጃና መለስተኛ 2 ደረጃ /ቤት፣ 2 ደረጃ ትምህርታቸውን በአርባ ምንጭ አጠቃላይ 2 ደረጃ /ቤት ተከታትለዋል፡፡ / ስምዖን የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በባዮሎጂ የትምህርት መስክ ሐምሌ 3/1984 /ም፣ የማስተርስ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተመሳሳይ የትምህርት መስክ ሐምሌ 2/1991 / እንዲሁም 3 ዲግሪያቸውን ቤልጂየም ሀገር ከሚገኘው አንተወርፕ ዩኒቨርሲቲ ..  የካቲት 25/2016 ‹‹Terrestrial Ecology›› የትምህርት ዘርፍ አግኝተዋል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

1985-1991 / ድረስ በተለያዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና በአርባ ምንጭ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም በመምህርነት፣ 1992-1996 በጂቲ ፕሮጀክት ባለሙያ በመሆን የሰሩት / ስምዖን አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን ነሐሴ 24/1996 / ተቀላቅለዋል፡፡ ከመማር ማስተማር፣ ምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ሥራቸው ባሻገር በተለያዩ የኃላፊነት መስኮች ዩኒቨርሲቲውን ያገለገሉት / ስምዖን ከሐምሌ 1/1997-መጋቢት 1/1999 / የተከታታይ ትምህርት ማስተባበሪያ ኃላፊ፣ ከግንቦት 19/2000 /-ሐምሌ 19/2001 / የጥናት፣ ምርምርና ሕትመት ማስተባበሪያ ኃላፊ፣ ከሐምሌ 20/2001 /- ጥር 8/2004 / የአስተዳደርና ልማት /ፕሬዝደንት፣ ከግንቦት 23/2008 /- ሕዳር 9/2010 / የምርምር ዳይሬክተር፣ ከሕዳር 10/2010- ጥር 30/2013 / ድረስ የምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት /ፕሬዝደንት በመሆን ዩኒቨርሲቲውን አገልግለዋል፡፡

ከነሐሴ 25/2012 / ጀምሮ የተባባሪ ፕሮፌሰርነት አካዳሚክ ማዕረግ ያገኙት / ስምዖን ከግንቦት 20/2017 / ጀምሮ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ዲን በመሆን ሕይታቸው እስካለፈበት ዕለት ድረስ አገልግለዋል፡፡

/ ስምዖን ባለትዳርና የአንድ ወንድና የሁለት ሴት ልጆች አባት ሲሆኑ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ 57 ዓመታቸው ነሐሴ 30/2017 / ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በዶ/ ስምዖን ሽብሩ ኅልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን እየገለጸ ለሟች ቤተሰቦች፣ የሥራ ባልደረቦች፣ ጓደኞችና ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ መጽናናትን ይመኛል፡፡

የቀብር ሥነ-ሥርዓታቸው ነገ ቅዳሜ ጳጉሜ 1/2017 / 8 ሰዓት በአርባ ምንጭ መድኃኒዓለም ካቴድራል የሚፈጸም ይሆናል፡፡

 

ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-

ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/

ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university

ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityccd/

ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA

 

የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ /ቤት