የሁሉም ተማሪዎች የሬጅስትራርና አሉምናይ ፋይል መሠረታዊ መረጃዎችን መያዝ እንዳለበት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡  በመሆኑም በሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች (ሪሚዲያል፣ ቅድመ-ምረቃ እና ድህረ-ምረቃ) የምትገኙ መደበኛ እና መደበኛ ያልሆናችሁ ተማሪዎች፣ እስከ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 . ድረስ የሚከተሉትን መረጃዎች በዩኒቨርሲቲው የኤስ.ኤም.አይ.ኤስ (SMIS) ሥርዓት ውስጥ እንድታስገቡ በጥብቅ እናሳስባለን፡-

  • የፋይዳ (Digital ID) ፋን ቁጥር
  • የግብር ከፋይ መለያ (TIN) ቁጥር
  • የአማርኛ ስም (ከነ አያት)
  • የትውልድ ዘመን (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር)

ማሳሰቢያ፡- ይህንን መረጃ በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማታጠናቅቁ ተማሪዎች፣ በቀጣይ በምረቃ ሂደትም ሆነ በሌሎች የሬጅስትራር አገልግሎቶች ላይ ለሚፈጠሩ ክፍተቶች ዩኒቨርሲቲው ኃላፊነት የማይወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አሉምናይ ዳይሬክቶሬት