- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህራንና ሐኪሞች አማካኝነት በጎፋ ዞን ከሚገኙ ወረዳዎች ለተወጣጡ 60 የህክምና ባለሙያዎች በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ መከላከል፣ ቁጥጥርና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከግንቦት 4-5/2012 ዓ/ም ድረስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የቆየ ሥልጠና በሳውላ ከተማ ተሰጥቷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከጎፋ ዞን ለተወጣጡ 60 ህክምና ባለሙያዎች በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ
- Details
While COVID-19 continues to spread the trail of catastrophe all across that has literally halted the wheels of economic activities leaving many without monetary and other resources at this critical time, in such situation, AMU’s Community Service Directorate is assuaging the sufferings of poor, homeless and elders in Gamo Zone by distributing some public protection gears, cereals, other eatables, etc. in its own way.
Read more: Coronavirus: AMU creating awareness, distributing aid to needy
- Details
ባሉበት
ውድ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ፣ ለመላዉ ዓለምም ሆነ ለሀገራችን ሰው ልጅ ሁሉ በሕይወት ለመኖር እጅግ ከፍተኛ ስጋት ያመጣዉ የኮቭድ-19 መከሰት ምክንያት ለሕዝብና ለሀገር ደህንነት ታስቦ በትኩረት እየተሠራ ካለዉ አንጻር በሀገራችን የሁሉም ትምህርት ደረጃ ተማሪዎች ወላጅ ወይም ቤተሰብ ዘንድ እንዲቆዩ በተደረገዉ ሂደት ከመጋቢት 19 እስከ 21/2012 ባሉት ቀናት ከዩኒቨርሲቲዉ ግቢ ወጥታችሁ ወደየቤተሰቦቻችሁ ዘንድ ከሄዳችሁበት ቀን ጀምሮ እንደምን አላችሁ? ውድ ተማሪዎች የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ 6ቱም ግቢዎች የሚሞቁትና የሚያምሩት እናንተ ስትኖሩበትና በግቢያችሁ ወዲያ ወዲህ (ከዶርም ወደ ክፍል፣ ከክፍል፣ ወደ ላይብራሪና ማጥኛ ቦታዎች፣ ወደ ሻይ/ቡና ወይም መዝናኛ ቦታዎች፣ ወደ አቢያተክርስቲያናትና መስጂዶች ከዚያም ወደ ግቢ፣ ወደ ከተማና ከዚያም ወደ ግቢያችሁ) ሽርጉድ እያላችሁ ስትመላለሱ ብቻ ነዉ፡፡ በክረምት ዕረፍት ለሁለት ወራት ወደ ቤተሰብ ስትሄዱ የክረምት ተማሪዎች ይተኩ ነበር፡፡ አሁን ግን ማንም ተማሪ የለም፡፡ የትምህርት ቤት/ተቋም ትልቁ የውበት ምንጭና ሕይወት ተማሪ ነዉ፡፡
Read more: ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጽ/ቤት የተላለፈ መልዕክት ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ
- Details
In order to complement the ongoing global efforts to study and understand the catastrophic implications of COVID-19, Arba Minch University acting on the directive of Ministry of Science and Higher Education has constituted a Research Council that will soon launch specific research projects to study broader aspects that were left totally upended in the wake of Corona virus outbreak in recent times.
Read more: Special Research Council to conduct COVID-19 related research
- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና በሽታን ስጋት ተከትሎ በአርባ ምንጭ ከተማ ለተቋቋመው ለይቶ ማቆያ ማዕከል የአልጋ፣ የፍራሽና የአንሶላ ቁሳቁሶች ድጋፍ አድርጓል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በተለምዶ ኩልፎ ካምፓስ ተብሎ በሚታወቀው የግብርና ሳይንስ ኮሌጅ የሚገኙ የተማሪ ማደሪያዎችንም ለለይቶ ማቆያ ለማዋል የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ዶ/ር የቻለ ከበደ እንዳሉት የኮሮና በሽታን ለመከላከልና አስከፊ ጉዳት እንዳያደርስ በሚደረገው ጥረት ዩኒቨርሲቲው የበኩሉን ሚና እንደሚወጣና እየተወጣም መሆኑን ገልፀው ለለይቶ ማቆያው የተደረገው ድጋፍም የዚሁ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት ይህንን ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በአርባ ምንጭ ከተማ ቡቡ ሜዳ ለተቋቋመው ለይቶ ማቆያ ማዕከል የቁሳቀስ ድጋፍ አደረገ
- AMU, Gamo Zone form Corona Task Force to contain transmission
- በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ስርጭት ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተቋቋመው ግብረ-ኃይል ማኅበረሰብ የማንቃት ቅስቀሳ እያካሄደ ነው
- በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ እና የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጆች የንጽህና መጠበቂያ ሳኒታይዘር በማዘጋጀት እያሰራጩ ነው
- የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቤኔፊት ሪያላይዝ (BENEFIT-REALISE) ፕሮግራም የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማስጠበቅ እየሠራ ይገኛል