አርባ ምንጭ ውኃ ቴክኖሎጂ ኢንሲቲትዩት በሥሩ ከሚገኙ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች፣ መምህራንና ቴክኒካል ሠራተኞች ጋር በ‹‹KPI›› ማስፈጸሚያ ዝርዝር ሃሳቦች፣ እየተሠሩ ባሉ የፕሮግራም ዕውቅና እና የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ ሥራዎች ዙሪያ ጥር 2/2017 ዓ.ም ውይይት አካሂዷል፡፡ በዕለቱ ኢንስቲትዩቱ በ2017 ዓ/ም የሚተገበር የቁልፍ አፈጻጸም ማሳያ ውል በሥሩ ከሚገኙ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ተፈራርሟል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
የኢንስቲትዩቱ ተ/ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ታምሩ ተሰሜ የውይይት መድረኩ በኢንስቲትዩቱ እየተከናወኑ በሚገኙ የፕሮግራም ዕውቅናና የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ ሥራዎች ዙሪያ ውይይት ለማካሄድና ግንዛቤ ለመፍጠር እንዲሁም ተግባራቱን የጋራ ለማድረግ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ በቅርቡ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር እንዲሁም የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ከም/ፕሬዝደንቶች ጋር በ2017 የሚፈጸም የቁልፍ ተግባራት ማሳያዎች ውል ተፈራርመዋል ያሉት ዶ/ር ታምሩ እንደ ኢንስቲትዩት በተሰጡ ቁልፍ ተግባራት ላይ በኢንስቲትዩቱ ሥር ከሚገኙ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ውል መፈራረምና ወደ ተግባር መግባት ሌላኛው የዕለቱ መርሃ ግብር ዓላማ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የኢንስቲትዩቱ አካዳሚክ ዳይሬክተር ዶ/ር አበበ ተመስገን ኢንስቲትዩቱ ካሉት 4 የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞች መካከል ሁለቱ የሀገር አቀፍ ብሎም ዓለም አቀፍ ዕውቅና እንዲያገኙ እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በውይይቱ በፕሮግራም ዕውቅና አሠራር ዙሪያ ግንዛቤ መፍጠርና የመምህራኑን ሚና ማሳወቅ እንደተቻለም አውስተዋል፡፡
ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የውይይት መድረኩ የኢንስቲትዩቱን ቁልፍ ተግባራት መለየት የተቻሉበት መሆኑን ተናግረው በዕቅድ የተያዙ ተግባራት እንዲሳኩ የበኩላቸውን ለመወጣት ቃል ገብተዋል፡፡ መሰል የውይይት መድረኮች ለተቋሙ የሥራ ስኬት በትብብር ለመሥራት የሚያግዙ በመሆናቸው ተጠናክረው ቢቀጥሉ ሲሉም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityccd/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA
የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት