አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከ “SNV-Rayee” ማስተርካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በአርባ ምንጭ ከተማ ለሚገኙ ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች የቢዝነስ ሃሳብ ውድድር ያዘጋጀ በመሆኑ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በውድድሩ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል፡፡
- የውድድሩ መስፈርት
 
- ዕድሜ፡ ከ18-35 ዓመት
 - ጾታ፡ አይለይም
 - አመልካቾች በአርባ ምንጭ ከተማ ነዋሪ መሆንና የቀበሌ ድጋፍ ወይም የታደሰ መታወቂያ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ከአርባ ምንጭ ከተማ ውጭ ለሆኑ ነዋሪዎች ውድድሩ አይመለከታቸውም
 - ሥራ አጥ ወጣቶች፣ የንግድ ሥራ የጀመሩ እንዲሁም በአነስተኛና ጥቃቅን የተደራጁ መወዳደር ይችላሉ
 - በአነስተኛና ጥቃቅን የንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ከሆኑ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል
 - አመልካቾች የሚወዳደሩበት የንግድ ሃሳብ ከዚህ በፊት በየትኛውም ዓይነት ንግድ ሃሳብ ውድድር ተወዳድረው ያልተሸለሙ መሆን አለባቸው
 - ወጣት ሴት ሥራ ፈጣሪዎች እና አካል ጉዳተኛ ወጣቶች ቅድሚያ እና ልዩ ትኩረት ይሰጣቸዋል
 - ወጣቶች በሚወዳደሩበት አዲስ የፈጠራ ሃሳባቸው ላይ የአእምሯዊ ንብረት ባለቤትነት ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው።
 
- የንግድ ሃሳብ ውድድር ዘርፎች
 
- በግብርና ዘርፍ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እና ሂደቶችን ያማከለ፣ ማምረት እና አቅርቦትን ጨምሮ አሁን ያለውን የምርት፣ የግብይት እና የማቀነባበር ችግሮች ለመቅረፍ የሚረዳ
 - በተመረጡ የዕሴት ሠንሰለቶች (የዶሮ እርባታ፣ የእንስሳት ማድለብ፣ የወተት ምርት፣ አትክልት እና ማር)
 - ጨርቃ ጨርቅ፣ አልባሳት እና አነስተኛ የእጅ ሥራዎች
 - የቀርከሃ እና የቆዳ ሥራ ዘርፎችን ጨምሮ ማንኛውም ዕሴት የሚጨምሩ ተግባራት
 
- ሽልማት
 
1ኛ ለወጡ 100,000 ብር
2ኛ ለወጡ 80,000 ብር
3ኛ ለወጡ 60,000 ብር
- የምዝገባ ቦታ
 
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ ጸጥታና ደኅንነት ቢሮ አጠገብ የሥራ ፈጠራ ልማትና ማበልጸጊያ ማዕከል ጽ/ቤት
- ለበለጠ መረጃ፡-
- ኢሜል፡ 
This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.  - ስልክ፡
 
 - ኢሜል፡ 
 
0910451411 ወይም
0996847492
- ምዝገባ የሚያልቅበት ቀን:- መስከረም 04/2016 ዓ/ም
 
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

