አርባ ምጭ ዩኒቨርሲቲ ለተመደቡ የሁለተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ስለፈተና አሰጣጥና በግቢ ውስጥ ስለሚኖራቸው ቆይታ ዛሬ ሐምሌ 24/2015 ዓ/ም ገለጻ (Orientation) ተሰጥቷል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በስድስቱም ካምፓሶቹ 6,546 ወንድ እና 4,857 ሴት በድምሩ 11,403 ተማሪዎች የተቀበለ ሲሆን በትምህርት ሚኒስቴር መርሃ ግብር መሠረት ፈተናውን ከሐምሌ 25/2015 ዓ/ም ጀምሮ የሚወስዱ ይሆናል፡፡ ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት