በ2018 ዓ.ም. የብሔራዊ የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (National Graduate Admission Test – NGAT) ለመውሰድ ለሚያቅዱ አመልካቾች በሙሉ፣ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለፈተናው የሚያዘጋጅ የNGAT የዝግጅት ቱቶሪያል ስልጠና እንደሚሰጥ በክብር ያሳውቃል።
1. የምዝገባ ጊዜ
- ከሐምሌ 14 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም.
- ምዝገባው በመስመር ላይ (Online) በሚቀርበው ሊንክ ይከናወናል።
ሊንክ: https://forms.gle/tsr2U5jKjchPqLgS6
2. የቱቶሪያል ስልጠና ቀን
- ከሐምሌ 22 እስከ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. (ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ዓርብ)
3. የቱቶሪያል ስልጠና ቦታ
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ዋና ግቢ
- ሕንፃ ቁጥር 105 (የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ሕንፃ)
4. የስልጠና መጀመሪያ ሰዓት
- ጠዋት 2፡30 ሰዓት
5. የምዝገባ ክፍያ
- 500 (አምስት መቶ) ብር
- የምዝገባ ክፍያው ወደ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የውስጥ ገቢ የንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000726844163 ገቢ መደረግ አለበት።
ማሳሰቢያ
- በቱቶሪያሉ ቀን የክፍያ ደረሰኙን ዋና ቅጂ (Hard Copy) ይዘው መቅረብ ይጠበቅብዎታል።
- የNGAT ፈተና በሐምሌ ወር መጨረሻ እንደሚሰጥ በዚህ አጋጣሚ እናሳውቃለን።
ድህረ ምረቃ ትምህርት ቤት ዳይሬክቶሬት
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የጥበብ ምንጭ!
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityccd/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA
የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት
