የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ነባር የ2015 እና የ2016 ባች ቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች መግቢያ ቀን እሁድ መስከረም 5/2017 ዓ.ም እንዲሆን ተወስኗል፡፡
በዚህ መሠረት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ነባር የ2015 እና የ2016 ባች ቅድመ ምረቃ መደበኛ ፕሮግራም ተማሪዎች እሁድ መስከረም 5/2017 ዓ.ም በየካምፓሶቻችሁ እንድትገኙ እያሳሰብን ሰኞ መስከረም 6/2017 ዓ.ም ከዚህ ቀደም በሀገራዊ ፕሮግራሞች መደራረብ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው ትምህርትና ፈተና የሚሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡- ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው አያስተናግድም፡፡
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት