- Details
በ2008 ዓ/ም ዩኒቨርሲቲው ለተቀላቀሉ 5700 አዲስ ገቢ ተማሪዎች ጥቅምት 28/2008 ዓ/ም የእንኳን ደህና መጣችሁ ፕሮግራም ተካሂዷል ፡፡ Click here to see the Pictures.
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ በመክፈቻ ንግግራቸው ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ዩኒቨርሲቲያችንን ምርጫ አድርጋችሁ የተቀላቀላችሁን ዉድ ተማሪዎቻችን እንኳን በደህና መጣችሁ ብለዋል፡፡በዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማርና የምርምር ሥራዎች እንዲሁም በማህበረሰብ አገልግሎቶች ተማሪዎች ቀጥተኛ ተሳታፊዎች በመሆንና ለትምህርታቸው ልዩ ትኩረት በመስጠት ለውጤት እንዲበቁ አሳስበዋል ፡፡ፕሬዝደንቱ አክለዉም ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲዉ የሚኖራቸዉ ቆይታ መልካም እንዲሆንላቸዉ ተመኝተዋል ፡፡
የዩኒቨርሲቲው የኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍስሃ በቀለ አዲስ ገቢ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው የሚኖራቸው ቆያታ የተሳካ እንዲሆን ዩኒቨርሲቲው የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ሁሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በጥራት ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል ፡፡
ተማሪዎቹ በሰጡት አስተያየት ዝግጅቱ ስለዩኒቨርሲቲዉ አገልግሎት አሰጣጥና ሌሎች ተያያዝ ጉዳዮች እንዲረዱ ያገዛቸዉ ከመሆኑ በተጨማሪ የእንግድነት ስሜት እንዳይፈጠርባቸዉ የረዳቸዉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡አያይዘዉም እንዲህ አይነት ደማቅ የእንኳን ደህና መጣችሁ ዝግጅት መደረጉ ዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች ያለዉ ክብር የሚያሳይና በቀጣይ በዩኒቨርሲቲው ለሚኖራችው ቆይታ ብሩህ ተስፋ የሚፈነጥቅ ነው ብለዋል ፡፡
በዕለቱ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል የተለያዩ የብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ሙዚቃና ዉዝዋዜዎች በማቅረብ ለፕሮግራሙ ድምቀት ሰጥቷል ፡፡
ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
- Details
የአንደኛውን የእድገትና ትራስፎርሜሽን ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የሁለተኛውን የእድገትና ትራስፎርሜሽን ረቂቅ ዕቅድ እንዲሁም ሌሎች ሀገራዊና ተቋማዊ አጀንዳዎችን ያካተተ ስልጠና ከመስከረም 7/2008 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞች እየተሰሠጠ ይገኛል፡፡ የስልጠናዉ ተሳትፎ በፎቶ የኢትዮጵያ ብሮድ ካስቲንግ ኮሮፖሬሽን ዘገባ
Read more: ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ መምህራን እና ሠራተኞች በሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ያተኮረ ልዩ ሥልጠና በመሰጠት ላይ ነው
- Details
Ministry of Education in association with Arba Minch University would be holding comprehensive orientation workshop for the academic staff, administrative personnel, senior and fresh students from September 18, 2015.
Read more: Govt. training for academic, admin and students from Sept. 18
- Details
በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች ሪፖርት የማድረጊያ ቀን ከመስከረም 24-25 ሲሆን ለነባር የዩኒቨርሲቲው ቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች የምዝገባ ቀን መስከረም 19-20 መሆኑን እያሳወቅን በተጠቀሰው ቀን በኣካል ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ እንታደርጉ እንገልፃለን፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ለነባር የድህረ-ምረቃ እና የቅድመ- ምረቃ የተከታታይና የርቀት ተማሪዎች ተማሪዎች ምዝገባ መስከረም 26-27/2008ዓ.ም መሆኑን እየገለፅን አዲስ ለሚመደቡ ወይም ለምንቀበላቸው የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎቸው ወደ ዩኒቨርሲቲው የመግቢያ ቀን በሌላ ማሰታወቂያ የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
Click here to download the full information.
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ሬጅስትራር ጽ/ቤት
- Details
Applied Entrepreneurship Education Program (AEEP), a three-year joint venture of Arba Minch University and Neu-Ulm University of Applied Sciences’ (HNU) completed its second term on Sept. 8, 2015.
Read more: AEEP: AMU-NHU’s venture completes term; prototypes developed