The globally coordinated master program tailor-made for the Ethiopian context, to facilitate the sustainable expansion of irrigation, ‘MSc in Irrigation Engineering and Management’, has been launched by Arba Minch University in October 2015. Partnering institutions like Mekelle and Bahir Dar universities are likely to launch it in the next academic year.

Academic Affairs Vice President, Dr Damtew Darza, will leave for Ghana to participate in a two-day workshop on Benchmarking Initiative - ‘Benchmarking of Applied Sciences Engineering & Technology Education in Africa’ is slated for 9th to 10th November 2015, at La Palm Royal Beach Hotel, Accra, Ghana.

2008 /ም ዩኒቨርሲቲውን ለተቀላቀሉ 5700 አዲስ ገቢ ተማሪዎች ጥቅምት 28/2008 /ም የእንኳን ደህና መጣችሁ ፕሮግራም ተካሂዷል ፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ በመክፈቻ ንግግራቸው ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ዩኒቨርሲቲያችንን ምርጫ አድርጋችሁ የተቀላቀላችሁን ውድ ተማሪዎቻችን እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማርና የምርምር ሥራዎች እንዲሁም በማህበረሰብ አገልግሎቶች ተማሪዎች ቀጥተኛ ተሳታፊዎች በመሆንና ለትምህርታቸው ልዩ ትኩረት በመስጠት ለውጤት እንዲበቁ አሳስበዋል፡፡ ፕሬዝደንቱ አክለዉም ተማሪዎቹ በዩኒቨርሲቲዉ የሚኖራቸዉ ቆይታ መልካም እንዲሆንላቸዉ ተመኝተዋል ፡፡

የዩኒቨርሲቲው ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍስሃ በቀለ አዲስ ገቢ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው የሚኖራቸው ቆይታ የተሳካ እንዲሆን ዩኒቨርሲቲው የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች ሁሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በጥራት ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ተማሪዎቹ በሰጡት አስተያየት ዝግጅቱ ስለ ዩኒቨርሲቲዉ አገልግሎት አሰጣጥና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች እንዲረዱ ያገዛቸው ከመሆኑም በተጨማሪ የእንግድነት ስሜት እንዳይፈጠርባቸዉም ያደረጋቸዉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አያይዘዉም እንዲህ አይነት ደማቅ የእንኳን ደህና መጣችሁ ዝግጅት መደረጉ ዩኒቨርሲቲው ለተማሪዎች ያለዉን ክብር የሚያሳይና በቀጣይ በዩኒቨርሲቲው ለሚኖራቸው ቆይታ ብሩህ ተስፋን የሚፈነጥቅ ነው ብለዋል፡፡

በዝግጅቱ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል የተለያዩ የብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ሙዚቃና ዉዝዋዜዎች በማቅረብ ለፕሮግራሙ ድምቀት ሰጥቷል፡፡

በማህበራዊና ስነ-ሰብ ኮሌጅ 118 አባላትን ያቀፈ የህግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ማህበር ጥቅምት 19/2008 ዓ/ም ተመስርቷል፡፡
የማህበሩ አባል ተማሪ ምስጋና ሙባረክ እንደገለፀችው የማህበሩ ዓላማ የዩኒቨርሲቲውንና የአካባቢውን ህብረተሰብ የህግ ግንዛቤ ማስጨበጥ፣ ነፃ የህግ ድጋፍ መስጠት፣ ህግን ባለማወቅ ከሚመጡ ችግሮች መጠበቅና ግጭቶችን ከፍርድ ቤት ይልቅ በአማራጭ የግጭት መፍቻ ዘዴዎች እንዲፈቱ ማስተማርና መደገፍ ነው፡፡ በተጨማሪም የህግ ተማሪዎችን በተለያዩ የማህበረሰብ አገልግሎት በማሳተፍ በዜጎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች በተለይም በፆታ እኩልነት በንድፈ ሃሳብ ደረጃ የቀሰሙትን ትምህርት በተግባር እንዲለማመዱና የህግ ግንዛቤያቸውን በማሳደግ በመልካም ስነ- ምግብር እንዲታነፁና የዩኒቨርሲቲውን ህግና ደንብ እንዲያከብሩ የሚደርግም ነው ፡፡
የህግ ትምህርት ክፍል ተጠሪ መ/ር ደረጀ ማሞ የማህበሩ መመስረት ተማሪዎች ራሳቸውን ችለው በማህበረሰብ አገልግሎት እንዲንቀሳቀሱና ዩኒቨርሲቲው በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጪ ተቋማት ጋር ግንኙነት እንዲመሠርት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል ፡፡
የጋሞ አካባቢ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ በቀለ በሻ ከህግ ሙያ ጋር ተያይዞ ትልቅ ኃላፊነት ፣ጊዜና ቦታ ሰጥቶ የመልካም አስተዳደር ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የበለጠ ከፋ እንዲል የህግ እውቀት ያላቸውን የሰው ኃይሎች  በብዛት ማፍራት ወሳኝነት እንዳለው ዓላማ አድርጎ እየሰራ ነው ሲሉ ተናግረዋል ፡፡ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲጎለብት የህግ የበላይነት ሊከበር የሚገባ ሲሆን  እነዚህ የዛሬዎቹ ተማሪዎች በጋራ ሆነው በአጠቃላይ ሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩ ከታች ጀምሮ ያለው ሃይል  ርብርብ ሲያደርግ ነው ብለዋል ፡፡
ተሳታፊዎቹ በሰጡት አስተያየት የህግ ት/ቤት ለማህበረሰቡ እያደረገው ያለው የነፃ የህግ ድጋፍ አገልግሎቶች፣ ሰዎች በቤታቸው ሆነው  በነፃ የህግ መንገድ የሬዲዮ ፕሮግራም ስለ ህግና ሰብዓዊ መብቶች  ምንነት እንዲረዱ የማድረጉ ተግባር የሚበረታታ እንደሆነና ተማሪዎቹ በማህበር መዋቀራቸው ይህንንና መሰል ተግባራቶችን በመወያየት የበለጠ እንዲሰሩ ያስችላቸዋል ሲሉ  ተናግረዋል ፡፡
በመጨረሻም ለማህበሩ መመስረት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ መ/ራንና ተማሪዎች የማበረታቻ የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡

Sahay Solar Association Africa (Sahay), University of Applied Sciences of Southern Switzerland (SUSPI), Arba Minch University, Southern Nations, Nationalities and People’s Region’s Gamo Gofa Zone office have entered into an agreement to install solar energy systems at 50 rural health centres that have no access to the national electricity grid on 14th April 2015 at Arba Minch.