የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ኅብረት በአባያ ክ/ከተማ በኩልፎ ቀበሌ ለተገኙ በርካታ አረጋዊያንና ወላጅ አጥ ሕፃናት የ2007 .ም የፋሲካ በዓልን በማስመልከት የምሳ ግብዣ አድርጓል፡፡

የሰጪ እጅ ሁሌም ከላይ ነው” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀውን የምሳ ግብዣ ያሰናዱት የተማሪዎች ኅብረት ፕሬዝደንት ተማሪ ጌትነት ዓለሙና የተማሪዎች ዲስፕሊን ተጠሪ ተማሪ ታመነ ዳኘው ናቸው፡፡ ተማሪ ጌትነት ባደረገው ንግግር የአ//ዩን ተማሪዎች ወክሎ ከታዳሚዎቹ መሃል በመገኘት በዓሉን ማክበሩ እንዳስደሰተውና ለወደፊትም በተመሳሳይ መልክና የበለጠ አቅም በመፍጠር በዓላትን በጋራ ለማሳለፍ እንደሚሠሩ ተናግሯል፡፡

በአባያ ክ ከተማ የኩልፎ ቀበሌ ወጣቶችና ስፖርት ዘርፍ ኃላፊ ወጣት ተክሌ ብርሃነገነት እና የአርባ ምንጭ ከተማ ሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ጽ ቤት ምኃላፊና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ ወጣት በላይ ግዛቸው የአዩ ተማሪዎች ኅብረት ያደረገውን ድጋፍ አመስግነው ለወደፊትም መሰል ትብብርና በጋራ የመሥራቱ ልምድ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ በዝግጅቱ መጨረሻም የአ ዩ ተማሪዎች ኅብረት ለተሳታፊ ስፖንሰሮች የተሰጠውን የምሥክር ወረቀት ወስዷል፡፡

 

በተመሳሳይም የአ//ዩ ከፍተኛ የአስተዳደር አካላት በ5ቱም ካምፓሶች ከተማሪዎች ጋር በመሆን የፋሲካን በዓል በድምቀት አክብረዋል፡፡ በዋናው ግቢ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ከሌሎች የአስተዳደር አካላት፣ የተማሪዎች ፕሬዝደንትና የተማሪዎች ተወካይ ኮሚቴዎች ጋር በመገኘት በዓሉ ደማቅ እንዲሆንና ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዳሉ እንዲሰማቸው የሚያደርግ ድባብ ፈጥረዋል፡፡

በሌሎቹም ካምፓሶች የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮሌጅ ዲኖችና የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እንዲሁም የተማሪዎች ተወካዮች ከተማሪዎች ጋር በመሆን በዓሉ በልዩ ድምቀት እንዲከበር አድርገዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ሰላም ፎረም ከግንቦት 22-23/2004 .ም በዋናው ግቢ በሰጠው ስልጠና በአምስቱም ግቢዎች የሚገኙ የተማሪዎች የሠላም ፎረም ፕሬዝደንቶችና አባል ተማሪዎች፣ አባል መምህራን፣ የካምፓስ አስተዳደሮች፣ የፀጥታና ደህንነት ሰራተኞች፣ዳይሬክተሮች፣ የጋሞ ጎፋ ዞን ፀጥታ አስተዳደር መምሪያ ተወካዮችና የሃይማኖት መሪዎች ተገኝተዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ስልጠናውን በንግግር ሲከፍቱ እንደገለጹት ከዚህ በፊት ከአገልግሎት አሰጣጥና ከሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ አሳማኝ ባልሆኑ ምክንያቶች ግጭቶች ይነሱ እንደነበር በማስታወስ ይህ ፎረም ከተቋቋመ በኋላ ግን በርካታ ችግሮችን በመቅረፍ ለሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡

ከደቡብ ክልል ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ተወክለዉ የመጡት አሰልጣኝ አቶ ኃይሉ ማቲዮስ በበኩላቸው በክልላችን በሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ይህ መዋቅር አበረታች እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡አቶ ማቲዮስ አያይዘዉ አደረጃጀቱ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ከመውረዱ በፊት ባለማወቅ ችግር ይፈጥሩ የነበሩ አንዳንድ ተማሪዎች ከጥፋታቸው ሙሉ በሙሉ በመዉጣት የሰላም አምባሳደር እስከ መሆን ደርሰዋል ብለዋል፡፡

የስልጠናዉ ትኩረት አቅጣጫ በዩኒቨርሲቲዉ ዉስጥ የሰላም ባህል እንዲጎለብት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ነዉ፡፡በወቅቱ ስለግጭት ምንነት፣መንስኤዎች፣አመላካች ሁኔታዎችና መፍትሄዎች ዙሪያ ሰፋ ያለ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎች አሰልጣኙ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በስልጠናው ማጠናቀቂያ ወቅት ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት አሁን ላይ በዩኒቨርሲቲው እየተካሄደ ያለዉ የመማር ማስተማር ሥራ አስደሳች መሆኑን በመጥቀስ ለወደፊቱም ሁሉም ተማሪ ለዩኒቨርሲቲዉ ሰላም በጋራ ኃላፊነት ሊወስድ ይገባል ብለዋል፡፡

በኮምፒዉተር ሳይንስ ትምህርት ክፍል ከ1-4ኛ አመት ድረስ በሚማሩ ተማሪዎች የተሰሩ 16 አዳዲስ የኮምፒዉተር ፕሮግራሞች በዋናዉ ግቢ እና በአባያ ግቢ ከግንቦት 11-12/2007 .ም ድረስ ለዕይታ ቀርበዋል፡፡

በዓውደ ርዕዩ ለዕይታ ከቀረቡ የኮምፒዉተር ፕሮግራሞች መካከል የዉጪ ሀገርና የሀገር ዉስጥ ጎቢኚዎች ባሉበት ሆነዉ በኢንተርኔት አማካኝነት ሆቴል ለመያዝ፣የአዉቶብስ ቲኬት ለመቁረጥ ፣ ስለቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎች መረጃ ማግኘት የሚያስችላቸዉና በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በተማሪዎች መመረቂያ ጽሁፎች ዝግጅት ወቅት የሚከሰቱ ኩረጃዎችን ለመቆጣጠር የሚያግዙ ፕሮግራሞች ተጠቃሾች ናቸዉ፡፡

የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ ኤግዚብሽኑን በጎበኙበት ወቅት እንደተናገሩት በኤግዚብሽኑ የቀረቡት የኮምፒዉተር ፕሮግራሞች ችግር ፈቺ ከመሆናቸዉ በተጨማሪ በተማሪዎች የግል ጥረት መሰራታቸዉ የሚበረታታ ነዉ፡፡ ዶ/ር ፈለቀ አክለዉ ተማሪዎች እንዲህ አይነት ሥራ መስራታቸዉ ከበስተጀርባቸዉ ጠንካራ መምህራን መኖራቸዉንና የዩኒቨርሲቲዉን የትምህርት አሰጣጥ ጥራት የሚያሳይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር ነጋሽ ዋጌሾ በበኩላቸዉ በኤግዚብሽኑ የቀረቡት የፈጠራ ሥራዎች ዓለም በኮምፒዉተር ዕዉቀት የደረሰበት ደረጃ ለመድረስ ከምናከናዉናቸዉ ተግባራት አንዱ አካል መሆኑን ጠቅሰዉ የፈጠራ ሥራዎቹ ወደ ተግባር ሊለወጡ የሚችሉ ናቸዉ ብለዋል፡፡

በአዉደ ርዕዩ ወቅት በተሳታፊዎች በተሰጠዉ ድምጽ አሸናፊ የሆነዉ በተማሪዎች መመረቂያ ጽሁፎች ዝግጅት ወቅት የሚከሰቱ ኩረጃዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችል ፕሮግራም በመስራት ለዕይታ ያቀረበዉ-4ኛ አመት ተመራቂ ተማሪ አቤል ተመስገን ነዉ፡፡ተማሪ አቤል እነደተናገረዉ ተመራቂ ተማሪዎች መመረቂያ ጽሁፎቻቸዉን በሚያቀርቡበት ወቅት በፊት የተመረቁ ተማሪዎች ከሰሯቸዉ ሥራዎች በተወሰነ መልኩ ኮርጀዉ ስለሚያቀርቡ በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ተማሪዎች የተሰሩ ፕሮጀክቶች አንዳንዶቹ ተመሳሳይነት ይታይባቸዋል፡፡ ስለዚህ እሱ የሰራዉ የኮምፒዉተር ፕሮግራም በኢኒስቲትዩቱ የተሰሩ ፕሮጀክቶችን በጠቅላላ መዝግቦ መያዝ ስለሚያስችል ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ሲመጡ በቀላሉ ለይቶ ያሳዉቃል፡፡ኩረጃ በአንድ የኒቨርሲቲ ብቻ የማይወሰን አለም አቀፋዊ እና ሀገር አቀፋዊ ባህሪ ስላለዉ አሁን የሰራዉን ፕሮጀክት በዚህ ደረጃ የማሳደግ ህልም እንዳለዉም ተማሪ አቤል አስምሮበታል፡፡

በአዉደ ርዕዩ መዝጊያ ስነ-ስርአት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲዉ መምህራን፣ተማሪዎች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በሰጡት አስተያየት እንዲህ አይነት አዉደ ርዕይ መካሄዱ ሌሎችንም ተማሪዎች የሚያነሳሳ መሆኑን በመጥቀስ የአዉደርዕዩ አቅራቢ ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን ትምህርት በተግባር አሳይተዋል ብለዋል፡፡



የግንቦት 20 ሃያ አራተኛ አመት የድል በዓል በዋናው ግቢ ግንቦት 26/2007 .ከብተና ስጋት ወደ ለዉጥ አብነት የተሸጋገረች ሀገር - ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በድምቀት ተከበረ፡፡

የኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍስሃ በቀለ የግንቦት 20 ፍሬዎችን በተመለከተ ዘርዘር ያለና ሁሉንም ዘርፎች የዳሰሰ የመወያያ ሰነድ ለታዳሚዎች አቅርበዉ ጠለቅ ያለ ዉይይት ተደርጎበታል፡፡በሰነዱ ከግንቦት 20 ድል በኋላ በሀገራችን በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ ፣በመሰረተ ልማት ፣ በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እና በሰላምና የውጭ ግንኙነት ዘርፎች የተመዘገቡ ድሎች ተዳስሰዋል፡፡

ሰነዱን መሰረት በማድረግ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት ከግንቦት 20 ድል ወዲህ በሀገሪቱ የብሄር፣ የቋንቋ ፣ የባህል፣ የጾታ እና የሃይማኖት ነፃነቶች የተከበሩ ሲሆን በኢኮኖሚ ዕድገት ረገድም አለም ባንክና ሌሎች አለም-አቀፋዊ ተቋማት የመሰከሩለት እድገት የተመዘገበ መሆኑን ጠቅሰዉ እኛም የአይን እማኞች ነን ብለዋል፡፡በተለይም በትምህርትና በጤና ተቋማት ግንባታና ተደራሽነት እንዲሁም በመንገድ ግንባታ፣በቴሌኮሙኒኬሽንና በመብራት ኃይል አቅርቦት የተመዘገቡ ለዉጦች ለሌሎች ሀገራትም ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም አስተያየት ሰጪዎች የተጀመረዉን የህዳሴ ጉዞ ማስቀጠል የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

በበአሉ አከባበር ስነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝደንት ዶ/ር ፈለቀ ወልደየስ እንደገለፁት ግንቦት 20 ለመላዉ ኢትዮጵያዊያን አንድ የጨለማ ምዕራፍ ተዘግቶ ሌላ አዲስ ብርሃን ፈንጣቂ ምዕራፍ የተጀመረበት ነዉ፡፡በመሆኑም የሀገራችን ህዝቦች በሽምቅ ውጊያ፣በግድያ፣በአፈናና ዉምብድና ከመሰቃየት ወጥተዉ ወደ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ ተሸጋግረዋል፡፡

የጋሞ ጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጥላሁን ከበደ በበኩላቸዉ የትግሉ ሰማዕታት የህዝብን አጀንዳ አንግበው ወደ ትግሉ ሲገቡ ለራሳቸው እንደማያልፍላቸውና የህይወት መስዋዕትነት ሊከፍሉ እንደሚችሉ ቢያውቁም ለመጪው ትውልድ ብርሃንን ይፈነጥቁ ዘንድ ተሰውተዋል ብለዋል፡፡ በመሆኑም የዛሬዉ ትዉልድ የህዳሴ ጎዳና ላይ ያለች ሰላማዊ ሀገር በመረከቡ ዕድለኛ ስለሆነ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ሁሉ በአግባቡ በመወጣት ሀገራችን እየተገበረች ለምትገኘዉ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ጉዞ የጀርባ አጥንት መሆን አለበት ሲሉም ተደምጠዋል፡፡በመጨረሻም የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሀገራችን ከግብርና መር ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ የምታደርገዉን ሽግግር በመማር-ማስተማር፣በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ከወትሮዉ በበለጠ እንዲደግፍ አሳስበዋል፡፡

የዩኒቨርሲቲዉ ከፍተኛ አመራሮች፣የአስተዳደርና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች፣መምህራንና ተማሪዎች በበአሉ ላይ የተገኙ ሲሆን የጋሞ ጎፋ ዞን ባህላዊ ኪነት ባንድ የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን በማሰማት በአሉን አድምቋል፡፡

This year’s overall topper of Arba Minch University, Tarekegn Tumebo Kariba, is a humble son of a farmer; he is from Kambata Tembaro zone. He has encountered difficulties but didn’t give in on the contrary come out successful.