
- Details
ዶ/ር ኢንጂነር ቦጋለ ገብረማርያም በ1981 የመጀመሪያ ዲግሪ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ ‹‹Civil Engineering››፣ በ1986 ዓ/ም ድኅረ ምረቃ ዲፕሎማ (Post Graduate Diploma) በ‹‹Hydraulic Engineering (Hydro informatics)›› ኔዘርላድ ሀገር ከሚገኘው ‹‹International Institute for Infrastructural, Hydraulic and Environmental engineering (IHE), Delft››፣ በ1987 ዓ/ም ከዚሁ ተቋም በ‹‹Hydraulic Engineering (Hydro informatics)›› የማስተርስ ዲግሪ፣ በ2000 ዓ/ም ጀርመን ከሚገኝ ‹‹Freie University of Berlin›› በ‹‹Lake Hydrodynamics›› የትምህርት ዘርፍ የሦስተኛ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡
Read more: ዶ/ር ኢንጂነር ቦጋለ ገብረማርያም የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝደንት ተወካይ

- Details
ፕ/ር ጳውሎስ ታደሰ ከሐሮማያ ዩኒቨርሲቲ በፊዚክስ ማስተማር ዲግሪ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በፊዚክስ ማስተርስ ዲግሪ እንዲሁም ከሕንዱ አንድህራ ዩኒቨርሲቲ በፊዚክስ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን አግኝተዋል፡፡

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተቋማዊ ጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት እና የአካዳሚክ ፕሮግራሞች ግምገማና ትግበራ ዳይሬክቶሬት ለውኃ ቴክኖሎጂ እና ለቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የፕሮግራም ዕውቅና /Program Accreditation/ ሥራ ኮሚቴ አባላት ሀገር አቀፍ የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የፕሮግራም ዕውቅና አሰጣጥ ላይ ባዘጋጀው መገምገሚያ መስፈርት ዙሪያ ታኅሣሥ 2/2017 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥተዋል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: ለውኃ ቴክኖሎጂ እና ለቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የፕሮግራም ዕውቅና ሥራ ኮሚቴ አባላት ሥልጠና ተሰጠ

- Details
ዶ/ር ተክሉ ወጋየሁ ዛራ የሳይንስ ባችለር ዲግሪ በባዮሎጂ በ1997 ዓ.ም፣ የሳይንስ ማስተርስ ዲግሪ በባዮሜዲካል ሳይንስ በ2001 ዓ.ም እና የዶክትሬት ዲግሪ በትሮፒካል እና ተላላፊ በሽታዎች ትምህርት ዘርፍ በ2008 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡
Read more: ዶ/ር ተክሉ ወጋየሁ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ትብብር ም/ፕሬዝደንት ተወካይ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቪርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ማኅበረሰብ ጉድኝት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ማኅበረሰብ ተራድኦ ድርጅት ጋር በመተባበር ‹‹Spiritan Community Outreach Ethiopia - SCORE›› በተሰኘ ፕሮጀክት ላይ ለሚሠሩ ባለሙያዎች በፕሮጀክት ማኔጀመንትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከኅዳር 25-28/2017 ዓ/ም ሥልጠና ሰጥቷል ፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ