- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የጋሞ ዞን አስተዳደር በምርምርና ማኅበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የትብብር መግባቢያ ስምምነት መጋቢት 21/2013 ዓ/ም ተፈራርመዋል፡፡
በመግባቢያ ስምምነቱ ዞኑና ዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰቡን ሕይወት በዘላቂነት መቀየር በሚያስችሉ የምርምር፣ የማኅበረሰብ አገልግሎት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የአቅም ግንባታ ዘርፎች ላይ በጋራ እንደሚሠሩ ተቀምጧል፡፡ ስምምነቱ ለ4 ዓመታት የሚቆይ ሲሆን ሁለቱ አካላት የሰው ሀብት፣ ቁሳቁስና ፋይናንስ በጋራ እንደሚጠቀሙ በስምምነቱ ተጠቅሷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲና የጋሞ ዞን አስተዳደር በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
- Details
በኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴርና በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ አዘጋጅነት 9ኛው ‹‹የሕክምና ት/ቤቶች ካውንስል በኢትዮጵያ›› ጉባዔ ከመጋቢት 16-17/2013 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ፓራዳይዝ ሎጅ አካሂዷል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ፖሊሲ፣ ስትራቴጂዎች፣ ፕሮግራሞች፣ የዘርፉ የ10 ዓመት የልማት ፍኖተ ካርታና ሌሎች ተያያዥ ሰነዶች ዙሪያ እየተሰጠ የሚገኘው ሥልጠናዊ ውይይት በዩኒቨርሲቲው ካምፓሶች እየተካሄደ ነው፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በዩኒቨርሲቲው 2ኛው ዙር የከፍተኛ ትምህርት ፐሊሲ፣ ስትራቴጂዎችና የ10 ዓመት የልማት ፍኖታ ካርታ ሥልጠና እየተካሄደ ነው
- Details
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ110ኛ በሀገራችን ለ45ኛ ጊዜ የተከበረው ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን ‹‹የሴቶችን መብት የሚያከብር ማኅበረሰብ እንገንባ›› በሚል መሪ ቃል መጋቢት 8/2013 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ተከብሯል፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ዳምጠው ዳርዛ በመክፈቻ ንግግራቸው ሴቶች የኅብረተሰቡ ግማሽ አካል በመሆናቸው በአንድ ሀገር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ጉልህ ሚና ሊኖራቸው ይገባል ብለዋል፡፡ በተለያዩ ተፅዕኖዎች ምክንያት የሴቶች ተሳትፎ ከወንዶች ጋር ሲነፃፀር ያነሰ ነው ያሉት ፕሬዝደንቱ አሁን በደረስንበት የዕድገት ደረጃ በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገራችን በሁሉም መስኮች የሴቶች ተሳትፎ በመጠንና በውጤታማነት ትልቅ ዕድገት እያሳየ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲውን ለሴት ተማሪዎች ምቹ ለማድረግ ሁሉም በትብብር መሥራት እንደሚጠበቅበትም ፕሬዝደንቱ አሳስበዋል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
‹‹የጠራ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ፖሊሲ፣ ስትራቴጂ፣ ዕቅድ፣ ፕሮግራሞችና ቁልፍ የውጤት አመላካቾች ግንዛቤና ትግበራ ለኢትዮጵያ ዕደገት፣ ልማትና ብልፅግና›› በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 10/2013 ዓ/ም ጀምሮ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በዋናው ግቢና ሳውላ ካምፓስ ከሚገኙ የካውንስል አባላትና ሠራተኞች ጋር የአሠልጣኝነት ሥልጠናዊ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ