- Details
ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝደንት ለመምረጥ በ19/12/2014 ዓ.ም በወጣው የኃላፊነት ቦታ ማስታወቂያ መሠረት ከተመዘገቡ ተወዳዳሪዎች ዝቅተኛውን መስፈርት በማሟላት የቀረቡ ተወዳዳሪዎች በመመሪያው መሠረት የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት እና ነባር መምህራን ወይም ተመራማሪዎች በተገኙበት የስትራቴጅክ ዕቅድ ገለጻ የሚደረግ ስለሆነ የኢንስቲትዩቶች፣ የኮሌጆች እና የት/ቤቶች ዲኖችና ሳይንቲፊክ ዳይሬክተሮች እንዲሁም የአስተዳደር ዳይሬክተሮች ከየዘርፋችሁ የካውንስል አባላት እና ከየትምህርት ክፍሉ አንድ አንድ ነባር/Senior/ መምህር ወይም ተመራማሪ ይዛችሁ በ5/03/2015 ዓ.ም 2፡3ዐ በዋናው ግቢ መግቢያ በር አካባቢ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ እንድትገኙ በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡
Read more: ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝደንትነት ውድድር የስትራቴጅክ ዕቅድ ገለፃ ተሳታፊዎች ጥሪ ማስታወቂያ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ዳይሬክቶሬት አማካኝነት በምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርገው የተዘጋጁ 35 ንድፈ-ሃሳቦች ቀርበው ከጥቅምት 24-25/2015 ዓ/ም ግምገማ ተካሂዶባቸዋል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: በምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ዘርፎች ላይ ያተኮሩ የምርምርና የማኅበረሰብ ጉድኝት ንድፈ-ሃሳቦች ተገመገሙሙ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጽ/ቤት ከዩኒቨርሲቲው ለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ለዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት ግምገማዊ የሥልጠና መድረክ ጥቅምት 22/2015 ዓ/ም አዘጋጅቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
- Details
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ በሂሳብ ት/ክፍል በ“Operation Research” ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር ሀብታሙ ፀጋዬ ነገ ቅዳሜ ኅዳር 03/2015 ዓ.ም ከረፋዱ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በዓባያ ካምፓስ በፒ.ኤች.ዲ. አዳራሽ እንዲሁም በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በማኔጅመንት ት/ክፍል በ“Marketing Management” ትምህርት ፕሮግራም የ3ኛ ዲግሪ ተማሪ ዕጩ ዶ/ር ስንታየሁ አሰፋ ረቡዕ ኅዳር 7/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በዋናው ግቢ መሰብሰቢያ አዳራሽ የመመረቂያ ፅሑፎቻቸውን በማቅረብ የሚያስገመግሙ ይሆናል፡፡ በመድረኩም የውጭና የውስጥ ገምጋሚዎችና አማካሪዎች ይገኙበታል፡፡
- Details
ትምህርት ሚኒስቴር ከሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ለተወጣጡ የመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ ዳይሬክተሮችና የሲስተም አስተዳደር ባለሙያዎች ‹‹Federated Identity System and Educational Roaming›› በሚል ርዕስ ከጥቅምት 24-26/2015 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: ለመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ ዳይሬክተሮችና የሲስተም አስተዳደር ባለሙያዎች ሥልጠና ተሰጠ

