
- Details
የዩኒቨርሲቲው የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ለዓባያ፣ ጫሞና ነጭ ሳር ካምፓስ የአስተዳደር ሠራተኞች የጾታና የሥርዓተ ጾታ ምንነት፣ የጾታዊ ጥቃቶች ምንነትና ዓይነቶች፣ ጾታዊ ጥቃቶችን መከላከያ መንገዶች እና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ ከግንቦት 02-03/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ የእግር ኳስ ክሂሎት ላላቸው በአርባ ምንጭ አካባቢ ከሚገኙ የተለያዩ የስፖርት ማዕከላትና ትምህርት ቤቶች ለተመለመሉ ከ17 ዓመት በታች ለሆኑ 60 ታዳጊዎች ሚያዝያ 28/2014 ዓ/ም የተለያዩ የእግር ኳስ ቁሳቁሶችን አበርክቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የእግር ኳስ ክሂሎት ላላቸው ከአርባ ምንጭና አካባቢው ለተመለመሉ ታዳጊዎች የተለያዩ የእግር ኳስ ቁሳቁሶች አበረከተ

- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረትና የሰላም ፎረም ከዩኒቨርሲቲው ጋር በመተባበር በ2014 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርሲቲው ለተቀላቀሉ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ከግንቦት 1-2 /2014 ዓ/ም አቀባበል አድርገዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ

- Details
የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግና ምቹ የገበያ ዕድል እንዲያገኙ ለማድረግ በተመሠረተው ዓለም አቀፍ ድርጅት ‹‹Vita›› ስር በኬኒያ ሀገር የተቋቋሙት የ‹‹Dream Team›› አባላት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለተቋቋሙት አቻ የ‹‹Dream Team›› አባላት፣ ለግብርና ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች ከሚያዝያ 24-26/2014 ዓ/ም በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በ‹‹PlantVillage›› እና ‹‹PlantVillageNuru›› ሶፍትዌር መተግበሪያ (Software Application) አጠቃቀም ዙሪያ በንድፈ ሃሳብና በተግባር የተደገፈ ሥልጠና ሰጥተዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ