- Details
የማኅበራዊ ሣይንስና ስነ- ሰብ ኮሌጅ ከጂኦግራፊና አካባቢ ጥናት የትምህርት ክፍል እና ከኮሌጁ ማህበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ቢሮ ጋር በመተባበር ‹‹Threats and Prospects of Natural Forest in Arba Minch›› በሚል ርዕስ ባከናወነው የቅድመ-ዳሰሳ ጥናት ላይ የአንድ ቀን የባለድርሻ አካላት ዓውደ ጥናት አካሂዷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
Read more: የአርባ ምንጭ የተፈጥሮ ደንን ለመታደግ የተከናወነ የቅድመ ዳሰሳ ጥናት ውይይት
- Details
የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የምርምር ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የመምህራንን የምርምር አቅም የሚያጎለብትና የምርምር ሥራ ጥራትን የሚያሳድግ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ከመጋቢት 21 - 24/2008 ዓ/ም ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
በሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የማህበረሰብ አገልግሎት ማስተባበሪያ ጽ/ቤትና በህክምና ላብራቶሪ ትምህርት ክፍል አዘጋጅነት የወባ በሽታ የቤተ-ሙከራ ምርመራ ውጤት ጥራትን ለማስጠበቅ ከመጋቢት 12-15 /2008 ዓ/ም ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
ዩኒቨርሲቲው በህክምና ዶክትሬት 47 እንዲሁም በስነ ህንጻና ከተማ ፕላን 57 በድምሩ 104 ተማሪዎች የካቲት 26/2008 ዓ.ም አስመርቋል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡
- Details
የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ከደቡብ ኦሞ፣ ከሰገን አካባቢ ህዝቦች፣ ከወላይታና ከዳውሮ ዞኖች ለተወጣጡ ከ60 በላይ የጤና ጣቢያና የሆስፒታል ባለሙያዎች የስጋ ደዌ፣ የቲቢና የኤች አይ ቪ/ኤድስ በሽታዎችን ለመከላከል የሚያስችል ስልጠና ከየካቲት 27 - መጋቢት 10 /2008 ዓ/ም ለአስር ቀናት በሁለት ዙር ሰጥቷል፡፡ ምስሎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡




