- Details
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ምርምር ዳይሬክቶሬት ከማኅበራዊ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ፣ ከቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ እንዲሁም ከስነ ትምህርትና ስነ ባህርይ ሳይንስ እና ከሕግ ት/ቤት ጋር በመተባበር 8ኛውን ሀገር አቀፍ ምርምር ለልማት አውደ ጥናት ከግንቦት 05-06/2014 ዓ/ም አካሂዷል፡፡
- Details
AMU-IUC ፕሮግራም ለሁለተኛ ዙር ላወጣው የ3ኛ ዲግሪ ትምህርት ዕድል አመልካች ሴት መምህራን ግንቦት 4/2014 ዓ/ም የማነቃቂያ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
- Details
የዩኒቨርሲቲው የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ለዓባያ፣ ጫሞና ነጭ ሳር ካምፓስ የአስተዳደር ሠራተኞች የጾታና የሥርዓተ ጾታ ምንነት፣ የጾታዊ ጥቃቶች ምንነትና ዓይነቶች፣ ጾታዊ ጥቃቶችን መከላከያ መንገዶች እና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ ከግንቦት 02-03/2014 ዓ/ም የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጥቷል፡፡
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ የእግር ኳስ ክሂሎት ላላቸው በአርባ ምንጭ አካባቢ ከሚገኙ የተለያዩ የስፖርት ማዕከላትና ትምህርት ቤቶች ለተመለመሉ ከ17 ዓመት በታች ለሆኑ 60 ታዳጊዎች ሚያዝያ 28/2014 ዓ/ም የተለያዩ የእግር ኳስ ቁሳቁሶችን አበርክቷል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ
Read more: አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የእግር ኳስ ክሂሎት ላላቸው ከአርባ ምንጭና አካባቢው ለተመለመሉ ታዳጊዎች የተለያዩ የእግር ኳስ ቁሳቁሶች አበረከተ
- Details
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ኅብረትና የሰላም ፎረም ከዩኒቨርሲቲው ጋር በመተባበር በ2014 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርሲቲው ለተቀላቀሉ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ከግንቦት 1-2 /2014 ዓ/ም አቀባበል አድርገዋል፡፡ፎቶዎቹን ለማየት እዚህ ይጫኑ